وَمَا هُوَ بِقَوۡلِ شَيۡطَٰنٖ رَّجِيمٖ

እርሱም (ቁርኣን) የእርጉም ሰይጣን ቃል አይደለም፡፡


فَأَيۡنَ تَذۡهَبُونَ

ታዲያ ወዴት ትኼዳላችሁ?


إِنۡ هُوَ إِلَّا ذِكۡرٞ لِّلۡعَٰلَمِينَ

እርሱ የዓለማት መገሠጫ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡


لِمَن شَآءَ مِنكُمۡ أَن يَسۡتَقِيمَ

ከናንተ ቀጥተኛ መኾንን ለሻ ሰው (መገሰጫ ነው)፡፡


وَمَا تَشَآءُونَ إِلَّآ أَن يَشَآءَ ٱللَّهُ رَبُّ ٱلۡعَٰلَمِينَ

የዓለማት ጌታ አላህ ካልሻም አትሹም፡፡



الصفحة التالية
Icon