يَعۡلَمُونَ مَا تَفۡعَلُونَ

የምትሠሩትን ሁሉ የሚያውቁ፡፡


إِنَّ ٱلۡأَبۡرَارَ لَفِي نَعِيمٖ

እውነተኞቹ ምእምናን በእርግጥ በገነት ውስጥ ናቸው፡፡


وَإِنَّ ٱلۡفُجَّارَ لَفِي جَحِيمٖ

ከሓዲዎቹም በእርግጥ በገሀነም ውስጥ ናቸው፡፡


يَصۡلَوۡنَهَا يَوۡمَ ٱلدِّينِ

በፍርዱ ቀን ይገቧታል፡፡


وَمَا هُمۡ عَنۡهَا بِغَآئِبِينَ

እነርሱም ከርሷ ራቂዎች አይደሉም፡፡


وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا يَوۡمُ ٱلدِّينِ

የፍርድ ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?


ثُمَّ مَآ أَدۡرَىٰكَ مَا يَوۡمُ ٱلدِّينِ

ከዚያም የፍርዱ ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?


يَوۡمَ لَا تَمۡلِكُ نَفۡسٞ لِّنَفۡسٖ شَيۡـٔٗاۖ وَٱلۡأَمۡرُ يَوۡمَئِذٖ لِّلَّهِ

(እርሱ) ማንኛይቱም ነፍስ ለሌላይቱ ነፍስ ምንም ማድረግን የማትችልበት ቀን ነው፡፡ ነገሩም ሁሉ በዚያ ቀን ለአላህ ብቻ ነው፡፡



الصفحة التالية
Icon