إِنَّ ٱلَّذِينَ ءَامَنُواْ وَعَمِلُواْ ٱلصَّـٰلِحَٰتِ لَهُمۡ جَنَّـٰتٞ تَجۡرِي مِن تَحۡتِهَا ٱلۡأَنۡهَٰرُۚ ذَٰلِكَ ٱلۡفَوۡزُ ٱلۡكَبِيرُ

እነዚያ ያመኑና መልካም ሥራዎችንም የሠሩ ለእነርሱ ከሥሮቻቸው ወንዞች የሚፈሱባቸው ገነቶች አሏቸው፡፡ ይህ ታላቅ ማግኘት ነው፡፡


إِنَّ بَطۡشَ رَبِّكَ لَشَدِيدٌ

የጌታህ በኀይል መያዝ ብርቱ ነው፡፡


إِنَّهُۥ هُوَ يُبۡدِئُ وَيُعِيدُ

እነሆ እርሱ መፍጠርን ይጀምራል፤ ይመልሳልም፡፡


وَهُوَ ٱلۡغَفُورُ ٱلۡوَدُودُ

እርሱም ምሕረተ ብዙ ወዳድ ነው፡፡


ذُو ٱلۡعَرۡشِ ٱلۡمَجِيدُ

የዙፋኑ ባለቤት የላቀው ነው፡፡


فَعَّالٞ لِّمَا يُرِيدُ

የሚሻውን ሁሉ ሠሪ ነው፡፡


هَلۡ أَتَىٰكَ حَدِيثُ ٱلۡجُنُودِ

የሰራዊቶቹ ወሬ መጣልህን?


فِرۡعَوۡنَ وَثَمُودَ

የፈርዖንና የሰሙድ፤ (ወሬ)፡፡


بَلِ ٱلَّذِينَ كَفَرُواْ فِي تَكۡذِيبٖ

በእውነቱ እነዚያ የካዱት በማስተባበል ውስጥ ናቸው፡፡


وَٱللَّهُ مِن وَرَآئِهِم مُّحِيطُۢ

አላህም በዙሪያቸው (በዕውቀቱ) ከባቢ ነው፡፡


بَلۡ هُوَ قُرۡءَانٞ مَّجِيدٞ

ይልቁንም እርሱ የከበረ ቁርኣን ነው፡፡



الصفحة التالية
Icon