ٱلَّذِي يَصۡلَى ٱلنَّارَ ٱلۡكُبۡرَىٰ

ያ ታላቂቱን እሳት የሚገባው፡፡


ثُمَّ لَا يَمُوتُ فِيهَا وَلَا يَحۡيَىٰ

ከዚያም በእርሷ ውስጥ አይሞትም ሕያውም አይኾንም፡፡


قَدۡ أَفۡلَحَ مَن تَزَكَّىٰ

የተጥራራ ሰው በእርግጥ ዳነ፡፡


وَذَكَرَ ٱسۡمَ رَبِّهِۦ فَصَلَّىٰ

የጌታውንም ስም ያወሳና የሰገደ፡፡


بَلۡ تُؤۡثِرُونَ ٱلۡحَيَوٰةَ ٱلدُّنۡيَا

ይልቁንም ቅርቢቱን ሕይወት ትመርጣላችሁ፡፡


وَٱلۡأٓخِرَةُ خَيۡرٞ وَأَبۡقَىٰٓ

መጨረሻይቱ (ሕይወት) በላጭ ሁል ጊዜ ዘውታሪም ስትኾን፡፡


إِنَّ هَٰذَا لَفِي ٱلصُّحُفِ ٱلۡأُولَىٰ

ይህ በፊተኞቹ መጻሕፍት ውስጥ ያልለ ነው፡፡


صُحُفِ إِبۡرَٰهِيمَ وَمُوسَىٰ

በኢብራሂምና በሙሳ ጽሑፎች ውስጥ፡፡



الصفحة التالية
Icon