فِيهَا سُرُرٞ مَّرۡفُوعَةٞ

በውስጧ ከፍ የተደረጉ አልጋዎች አልሉ፡፡


وَأَكۡوَابٞ مَّوۡضُوعَةٞ

በተርታ የተኖሩ ብርጭቆዎችም፡፡


وَنَمَارِقُ مَصۡفُوفَةٞ

የተደረደሩ መከዳዎችም፡፡


وَزَرَابِيُّ مَبۡثُوثَةٌ

የተነጠፉ ስጋጃዎችም (አልሉ)፡፡


أَفَلَا يَنظُرُونَ إِلَى ٱلۡإِبِلِ كَيۡفَ خُلِقَتۡ

(ከሓዲዎች) አይመለከቱምን? ወደ ግመል እንዴት እነደተፈጠረች!


وَإِلَى ٱلسَّمَآءِ كَيۡفَ رُفِعَتۡ

ወደ ሰማይም እንዴት ከፍ እንደ ተደረገች!


وَإِلَى ٱلۡجِبَالِ كَيۡفَ نُصِبَتۡ

ወደ ተራራዎችም እንዴት እንደ ተቸከሉ!


وَإِلَى ٱلۡأَرۡضِ كَيۡفَ سُطِحَتۡ

ወደ ምድርም እንዴ እንደተዘረጋች (አይመለከቱምን?)


فَذَكِّرۡ إِنَّمَآ أَنتَ مُذَكِّرٞ

አስታውስም፤ አንተ አስታዋሽ ብቻ ነህና፡፡


لَّسۡتَ عَلَيۡهِم بِمُصَيۡطِرٍ

በእነርሱ ላይ ተሿሚ (አስገዳጅ) አይደለህም፡፡


إِلَّا مَن تَوَلَّىٰ وَكَفَرَ

ግን (ከእውነት) የዞረና የካደ ሰው፤


فَيُعَذِّبُهُ ٱللَّهُ ٱلۡعَذَابَ ٱلۡأَكۡبَرَ

አላህ ታላቁን ቅጣት ይቀጣዋል፡፡



الصفحة التالية
Icon