وَجِاْيٓءَ يَوۡمَئِذِۭ بِجَهَنَّمَۚ يَوۡمَئِذٖ يَتَذَكَّرُ ٱلۡإِنسَٰنُ وَأَنَّىٰ لَهُ ٱلذِّكۡرَىٰ

ገሀነምም በዚያ ቀን በተመጣች ጊዜ በዚያ ቀን ሰው (ጥፋቱን) ይገነዘባል፡፡ መገንዘብም ለእርሱ ከየቱ?


يَقُولُ يَٰلَيۡتَنِي قَدَّمۡتُ لِحَيَاتِي

«ዋ እኔ! ምነው በሕይወቴ (መልካምን ሥራ) ባስቀደምኩ ኖሮ» ይላል፡፡


فَيَوۡمَئِذٖ لَّا يُعَذِّبُ عَذَابَهُۥٓ أَحَدٞ

በዚያ ቀንም የርሱን አቀጣጥ አንድም አይቀጣም፡፡


وَلَا يُوثِقُ وَثَاقَهُۥٓ أَحَدٞ

የእርሱንም አስተሳሰር አንድም አያስርም፡፡


يَـٰٓأَيَّتُهَا ٱلنَّفۡسُ ٱلۡمُطۡمَئِنَّةُ

(ለአመነች ነፍስም) «አንቺ የረካሺው ነፍስ ሆይ!


ٱرۡجِعِيٓ إِلَىٰ رَبِّكِ رَاضِيَةٗ مَّرۡضِيَّةٗ

«ወዳጅ ተወዳጅ ኾነሽ ወደ ጌታሽ ተመለሺ፡፡


فَٱدۡخُلِي فِي عِبَٰدِي

«በባሮቼም ውስጥ ግቢ፡፡


وَٱدۡخُلِي جَنَّتِي

ገነቴንም ግቢ፤» (ትባላለች)፡፡



الصفحة التالية
Icon