وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا ٱلۡعَقَبَةُ

ዓቀበቲቱም (መውጣቷ) ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ?


فَكُّ رَقَبَةٍ

(እርሱ) ጫንቃን መልቀቅ ነው፡፡


أَوۡ إِطۡعَٰمٞ فِي يَوۡمٖ ذِي مَسۡغَبَةٖ

ወይም የረኃብ ባለቤት በኾነ ቀን ማብላት፡፡


يَتِيمٗا ذَا مَقۡرَبَةٍ

የዝምድና ባለቤት የኾነን የቲም፤


أَوۡ مِسۡكِينٗا ذَا مَتۡرَبَةٖ

ወይም የዐፈር ባለቤት የኾነን ድኻ (ማብላት ነው)፡፡


ثُمَّ كَانَ مِنَ ٱلَّذِينَ ءَامَنُواْ وَتَوَاصَوۡاْ بِٱلصَّبۡرِ وَتَوَاصَوۡاْ بِٱلۡمَرۡحَمَةِ

(ዐቀበቲቱን አልወጣም)፡፡ ከዚያም ከነዚያ ከአመኑትና በመታገስ አደራ ከተባባሉት፣ በማዘንም አደራ ከተባባሉት ሰዎች አልኾነም፡፡


أُوْلَـٰٓئِكَ أَصۡحَٰبُ ٱلۡمَيۡمَنَةِ

እነዚያ (ይህንን የፈጸሙ) የቀኝ ጓዶች ናቸው፡፡


وَٱلَّذِينَ كَفَرُواْ بِـَٔايَٰتِنَا هُمۡ أَصۡحَٰبُ ٱلۡمَشۡـَٔمَةِ

እነዚያም በአንቀጾቻችን የካዱት እነርሱ የግራ ጓዶች ናቸው፡፡


عَلَيۡهِمۡ نَارٞ مُّؤۡصَدَةُۢ

በእነርሱ ላይ የተዘጋች እሳት አልለች፡፡



الصفحة التالية
Icon