۞وَأَوۡحَيۡنَآ إِلَىٰ مُوسَىٰٓ أَنۡ أَسۡرِ بِعِبَادِيٓ إِنَّكُم مُّتَّبَعُونَ

ወደ ሙሳም «ባሮቼን ይዘህ ሌሊት ኺድ፡፡ እናንተ የሚከተሉዋችሁ ናችሁና» ስንል ላክን፡፡


فَأَرۡسَلَ فِرۡعَوۡنُ فِي ٱلۡمَدَآئِنِ حَٰشِرِينَ

ፈርዖንም በየከተሞቹ ሰብሳቢዎችን (እንዲህ ሲል) ላከ፡፡


إِنَّ هَـٰٓؤُلَآءِ لَشِرۡذِمَةٞ قَلِيلُونَ

«እነዚህ ጥቂቶች ጭፈሮች ናቸው፡፡


وَإِنَّهُمۡ لَنَا لَغَآئِظُونَ

«እነርሱም ለእኛ አስቆጪዎች ናቸው፡፡


وَإِنَّا لَجَمِيعٌ حَٰذِرُونَ

«እኛም ብዙዎች ጥንቁቆች ነን፤» (አለ)፡፡


فَأَخۡرَجۡنَٰهُم مِّن جَنَّـٰتٖ وَعُيُونٖ

አወጣናቸውም፡፡ ከአትክልቶችና ከምንጮች፡፡


وَكُنُوزٖ وَمَقَامٖ كَرِيمٖ

ከድልቦችም ከመልካም መቀመጫዎችም፡፡


كَذَٰلِكَۖ وَأَوۡرَثۡنَٰهَا بَنِيٓ إِسۡرَـٰٓءِيلَ

እንደዚሁ ለእስራኤል ልጆች አወረስናትም፡፡


فَأَتۡبَعُوهُم مُّشۡرِقِينَ

ፀሐይዋ ስትወጣም ተከተሉዋቸው፡፡


فَلَمَّا تَرَـٰٓءَا ٱلۡجَمۡعَانِ قَالَ أَصۡحَٰبُ مُوسَىٰٓ إِنَّا لَمُدۡرَكُونَ

ሁለቱ ጭፍሮችም በተያዩ ጊዜ የሙሳ ጓዶች «እኛ(የፈርዖን ሰዎች) የሚደርሱብን ነን» አሉ፡፡



الصفحة التالية
Icon