فَكُبۡكِبُواْ فِيهَا هُمۡ وَٱلۡغَاوُۥنَ

በውስጧም እነሱና ጠማሞቹ በፊቶቻቸው ተጥለው ይንከባለላሉ፡፡


وَجُنُودُ إِبۡلِيسَ أَجۡمَعُونَ

የሰይጣንም ሰራዊቶች መላውም (ይጣላሉ)፡፡


قَالُواْ وَهُمۡ فِيهَا يَخۡتَصِمُونَ

እነርሱም በእርሷ ውስጥ የሚከራከሩ ኾነው ይላሉ፡-


تَٱللَّهِ إِن كُنَّا لَفِي ضَلَٰلٖ مُّبِينٍ

በአላህ እንምላለን፤ እኛ በግልጽ መሳሳት ውስጥ ነበርን፡፡


إِذۡ نُسَوِّيكُم بِرَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ

(ጣዖቶቹን) በዓለማት ጌታ ባስተካከልናችሁ ጊዜ፡፡


وَمَآ أَضَلَّنَآ إِلَّا ٱلۡمُجۡرِمُونَ

አመጸኞቹም እንጅ ሌላ አላሳሳተንም፡፡


فَمَا لَنَا مِن شَٰفِعِينَ

ከአማላጆችም ለእኛ ምንም የለንም፡፡


وَلَا صَدِيقٍ حَمِيمٖ

አዛኝ ወዳጂም (የለንም)፡፡


فَلَوۡ أَنَّ لَنَا كَرَّةٗ فَنَكُونَ مِنَ ٱلۡمُؤۡمِنِينَ

ለእኛም አንዲት ጊዜ መመለስ በኖረችንና ከአማኞቹ በኾን እንመኛለን (ይላሉ)፡፡


إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَأٓيَةٗۖ وَمَا كَانَ أَكۡثَرُهُم مُّؤۡمِنِينَ

በዚህ ውስጥ አስደናቂ ግሳጼ አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡


وَإِنَّ رَبَّكَ لَهُوَ ٱلۡعَزِيزُ ٱلرَّحِيمُ

ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡



الصفحة التالية
Icon