إِنِّي لَكُمۡ رَسُولٌ أَمِينٞ

«እኔ ለናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡


فَٱتَّقُواْ ٱللَّهَ وَأَطِيعُونِ

«አላህንም ፍሩ ታዘዙኝም፡፡


وَمَآ أَسۡـَٔلُكُمۡ عَلَيۡهِ مِنۡ أَجۡرٍۖ إِنۡ أَجۡرِيَ إِلَّا عَلَىٰ رَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ

«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አለምናችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡


أَتَبۡنُونَ بِكُلِّ رِيعٍ ءَايَةٗ تَعۡبَثُونَ

«የምትጫወቱ ኾናችሁ በከፍተኛ ስፍራ ሁሉ ላይ ምልክትን ትገነባላችሁን


وَتَتَّخِذُونَ مَصَانِعَ لَعَلَّكُمۡ تَخۡلُدُونَ

«የውሃ ማጠራቀሚያዎችንና ሕንፃዎችንም ዘላለም መኖርን የምትከጅሉ ኾናችሁ ትሠራላችሁን


وَإِذَا بَطَشۡتُم بَطَشۡتُمۡ جَبَّارِينَ

«በቀጣችሁም ጊዜ ጨካኞች ኾናችሁ ትቀጣላችሁን


فَٱتَّقُواْ ٱللَّهَ وَأَطِيعُونِ

«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡


وَٱتَّقُواْ ٱلَّذِيٓ أَمَدَّكُم بِمَا تَعۡلَمُونَ

«ያንንም በምታውቁት (ጸጋ) ያጣቀማችሁን ፍሩ፡፡


أَمَدَّكُم بِأَنۡعَٰمٖ وَبَنِينَ

«በእንስሳዎችና በልጆች ያጣቀማችሁን፡፡


وَجَنَّـٰتٖ وَعُيُونٍ

«በአትክልቶችና በምንጮችም፡፡



الصفحة التالية
Icon