وَأَنذِرۡ عَشِيرَتَكَ ٱلۡأَقۡرَبِينَ

ቅርቦች ዘመዶችህንም አስጠንቅቅ፡፡


وَٱخۡفِضۡ جَنَاحَكَ لِمَنِ ٱتَّبَعَكَ مِنَ ٱلۡمُؤۡمِنِينَ

ከምእምናንም ለተከተሉህ ሰዎች ክንፍህን ዝቅ አድርግ፤ (ልዝብ ኹን)፡፡


فَإِنۡ عَصَوۡكَ فَقُلۡ إِنِّي بَرِيٓءٞ مِّمَّا تَعۡمَلُونَ

«እንቢ» ቢሉህም «እኔ ከምትሠሩት ንጹሕ ነኝ» በላቸው፡፡


وَتَوَكَّلۡ عَلَى ٱلۡعَزِيزِ ٱلرَّحِيمِ

አሸናፊ አዛኝ በኾነው (ጌታህ) ላይም ተጠጋ፡፡


ٱلَّذِي يَرَىٰكَ حِينَ تَقُومُ

በዚያ ለሶላት በምትቆም ጊዜ በሚያይህ፡፡


وَتَقَلُّبَكَ فِي ٱلسَّـٰجِدِينَ

በሰጋጆች ውስጥ መዘዋወርህንም (በሚያየው ጌታህ ላይ ተጠጋ)፡፡


إِنَّهُۥ هُوَ ٱلسَّمِيعُ ٱلۡعَلِيمُ

እነሆ እርሱ ሰሚው ዐዋቂው ነውና፡፡


هَلۡ أُنَبِّئُكُمۡ عَلَىٰ مَن تَنَزَّلُ ٱلشَّيَٰطِينُ

ሰይጣናት በማን ላይ እንደሚወርዱ ልንገራችሁን


تَنَزَّلُ عَلَىٰ كُلِّ أَفَّاكٍ أَثِيمٖ

በውሸታም ኀጢአተኛ ሁሉ ላይ ይወርዳሉ፡፡


يُلۡقُونَ ٱلسَّمۡعَ وَأَكۡثَرُهُمۡ كَٰذِبُونَ

የሰሙትን (ወደ ጠንቋዮች) ይጥላሉ፡፡ አብዛኞቻቸውም ውሸታሞች ናቸው፡፡



الصفحة التالية
Icon