فَٱسۡتَفۡتِهِمۡ أَهُمۡ أَشَدُّ خَلۡقًا أَم مَّنۡ خَلَقۡنَآۚ إِنَّا خَلَقۡنَٰهُم مِّن طِينٖ لَّازِبِۭ

ጠይቃቸውም፤ እነርሱ በአፈጣጠር ይበልጥ የበረቱ ናቸውን? ወይስ እኛ (ከእነርሱ በፊት) የፈጠርነው? (ፍጡር) እኛ ከሚጣበቅ ጭቃ ፈጠርናቸው፡፡


بَلۡ عَجِبۡتَ وَيَسۡخَرُونَ

ይልቁንም (በማስተባበላቸው) ተደነቅህ፤(ከመደነቅህ) ይሳለቃሉም፡፡


وَإِذَا ذُكِّرُواْ لَا يَذۡكُرُونَ

በተገሠጹም ጊዜ አይመለሱም፡፡


وَإِذَا رَأَوۡاْ ءَايَةٗ يَسۡتَسۡخِرُونَ

ተዓምርን ባዩም ጊዜ ለመሳለቅ ይጠራራሉ፡፡


وَقَالُوٓاْ إِنۡ هَٰذَآ إِلَّا سِحۡرٞ مُّبِينٌ

ይላሉም «ይህ ግልጽ ድግምት እንጂ ሌላ አይደለም፡፡


أَءِذَا مِتۡنَا وَكُنَّا تُرَابٗا وَعِظَٰمًا أَءِنَّا لَمَبۡعُوثُونَ

«በሞትንና ዐፈርና አጥንቶችም በኾን ጊዜ እኛ የምንቀሰቀስ ነን?


أَوَءَابَآؤُنَا ٱلۡأَوَّلُونَ

«የቀድሞዎቹ አባቶችንም? (ይላሉ)፡፡


قُلۡ نَعَمۡ وَأَنتُمۡ دَٰخِرُونَ

«አዎን እናንተ ወራዶች ሆናችሁ (ትነሳላችሁ)» በላቸው፡፡


فَإِنَّمَا هِيَ زَجۡرَةٞ وَٰحِدَةٞ فَإِذَا هُمۡ يَنظُرُونَ

እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት፡፡ እነርሱም ወዲያውኑ (ምን እንደሚፈጸምባቸው) ያያሉ፡፡


وَقَالُواْ يَٰوَيۡلَنَا هَٰذَا يَوۡمُ ٱلدِّينِ

«ዋ ጥፋታችን! ይህ የፍርዱ ቀን ነው» ይላሉም፡፡



الصفحة التالية
Icon