فَأَقۡبَلَ بَعۡضُهُمۡ عَلَىٰ بَعۡضٖ يَتَسَآءَلُونَ

የሚጠያየቁም ሆነው ከፊላቸው ወደ ከፊሉ ይመጣሉ፡፡


قَالَ قَآئِلٞ مِّنۡهُمۡ إِنِّي كَانَ لِي قَرِينٞ

ከእነርሱ የሆነ ተናጋሪ ይላል «እኔ ጓደኛ ነበረኝ፡፡


يَقُولُ أَءِنَّكَ لَمِنَ ٱلۡمُصَدِّقِينَ

«በእርግጥ አንተ ከሚያምኑት ነህን? የሚል፡፡


أَءِذَا مِتۡنَا وَكُنَّا تُرَابٗا وَعِظَٰمًا أَءِنَّا لَمَدِينُونَ

«በሞትንና ዐፈር አጥንቶችም በሆን ጊዜ እኛ በእርግጥ እንመረመራለን?» (የሚል)፡፡


قَالَ هَلۡ أَنتُم مُّطَّلِعُونَ

እናንተ ተመልካቾች ናችሁን? ይላል፡፡


فَٱطَّلَعَ فَرَءَاهُ فِي سَوَآءِ ٱلۡجَحِيمِ

ይመለከታልም፤ በገሀነም መካከልም (ጓደኛውን) ያየዋል፡፡


قَالَ تَٱللَّهِ إِن كِدتَّ لَتُرۡدِينِ

ይላል «በአላህ እምላለሁ፤ በእርግጥ ልታጠፋኝ ቀርበህ ነበር፡፡


وَلَوۡلَا نِعۡمَةُ رَبِّي لَكُنتُ مِنَ ٱلۡمُحۡضَرِينَ

«የጌታየም ጸጋ ባልነበረ ኖሮ ወደ እሳት ከሚቀርቡት እሆን ነበር፡፡»


أَفَمَا نَحۡنُ بِمَيِّتِينَ

(የገነት ሰዎች ይላሉ) «እኛ የምንሞት አይደለንምን?


إِلَّا مَوۡتَتَنَا ٱلۡأُولَىٰ وَمَا نَحۡنُ بِمُعَذَّبِينَ

«የመጀመሪያይቱ መሞታችን ብቻ ስትቀር፡፡ እኛም የምንቅቀጣ አይደለንምን?» (ይላሉ)፡፡



الصفحة التالية
Icon