فَرَاغَ إِلَىٰٓ ءَالِهَتِهِمۡ فَقَالَ أَلَا تَأۡكُلُونَ

ወደ አማልክቶቻቸውም ተዘነበለ፡፡ አለም፡- «አትበሉምን?»


مَا لَكُمۡ لَا تَنطِقُونَ

«የማትናገሩት ለናንተ ምን አላችሁ?»


فَرَاغَ عَلَيۡهِمۡ ضَرۡبَۢا بِٱلۡيَمِينِ

በኀይል የሚመታቸውም ሆኖ በእነርሱ ላይ በድብቅ ተዘነበለ፡፡


فَأَقۡبَلُوٓاْ إِلَيۡهِ يَزِفُّونَ

ወደእርሱም (ሰዎቹ) እየሮጡ መጡ፡፡


قَالَ أَتَعۡبُدُونَ مَا تَنۡحِتُونَ

አላቸው «የምትጠርቡትን ትግገዛላችሁን?»


وَٱللَّهُ خَلَقَكُمۡ وَمَا تَعۡمَلُونَ

«አላህ እናንተንም የምትሠሩትንም የፈጠረ ሲኾን፡፡»


قَالُواْ ٱبۡنُواْ لَهُۥ بُنۡيَٰنٗا فَأَلۡقُوهُ فِي ٱلۡجَحِيمِ

«ለእርሱም ግንብን ገንቡ በእሳት ነበልባል ውስጥ ጣሉትም» አሉ፡፡


فَأَرَادُواْ بِهِۦ كَيۡدٗا فَجَعَلۡنَٰهُمُ ٱلۡأَسۡفَلِينَ

በእርሱም ተንኮልን አሰቡ፡፡ ዝቅተኞችም አደረግናቸው፡፡


وَقَالَ إِنِّي ذَاهِبٌ إِلَىٰ رَبِّي سَيَهۡدِينِ

አለም «እኔ ወደ ጌታዬ ኼያጅ ነኝ፡፡ በእርግጥ ይመራኛልና፡፡»


رَبِّ هَبۡ لِي مِنَ ٱلصَّـٰلِحِينَ

ጌታዬ ሆይ! ከመልካሞቹ የሆነን (ልጅ) ስጠኝ፡፡



الصفحة التالية
Icon