إِنَّهُمۡ لَهُمُ ٱلۡمَنصُورُونَ

እነርሱ ተረጂዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡


وَإِنَّ جُندَنَا لَهُمُ ٱلۡغَٰلِبُونَ

ሰራዊቶቻችንም በእርግጥ አሸናፊዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡


فَتَوَلَّ عَنۡهُمۡ حَتَّىٰ حِينٖ

ከእነርሱም (ከመካ ከሓዲዎች) እስከ ጥቂት ጊዜ ድረስ ዙር (ተዋቸው)፡፡


وَأَبۡصِرۡهُمۡ فَسَوۡفَ يُبۡصِرُونَ

እያቸውም ወደፊትም (የሚደርስባቸውን) ያያሉ፡፡


أَفَبِعَذَابِنَا يَسۡتَعۡجِلُونَ

በቅጣታችንም ያቻኩላሉን?


فَإِذَا نَزَلَ بِسَاحَتِهِمۡ فَسَآءَ صَبَاحُ ٱلۡمُنذَرِينَ

በቀያቸውም በወረደ ጊዜ የተስፈራሪዎቹ ንጋት ከፋ!


وَتَوَلَّ عَنۡهُمۡ حَتَّىٰ حِينٖ

እነርሱንም እስከ (ጥቂት) ጊዜ ድረስ ተዋቸው፡፡


وَأَبۡصِرۡ فَسَوۡفَ يُبۡصِرُونَ

ተመልከትም በእርግጥም ያያሉ፡፡


سُبۡحَٰنَ رَبِّكَ رَبِّ ٱلۡعِزَّةِ عَمَّا يَصِفُونَ

የማሸነፍ ጌታ የሆነው ጌታህ ከሚሉት ሁሉ ጠራ፡፡


وَسَلَٰمٌ عَلَى ٱلۡمُرۡسَلِينَ

በመልክተኞቹም ላይ ሰላም ይኹኑ፤


وَٱلۡحَمۡدُ لِلَّهِ رَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ

ምስጋናም ለዓለማት ጌታ ለአላህ ይሁን፡፡



الصفحة التالية
Icon