يَسۡـَٔلُونَ أَيَّانَ يَوۡمُ ٱلدِّينِ

የዋጋ መስጫው ቀን መቼ እንደ ኾነ ይጠይቃሉ፡፡


يَوۡمَ هُمۡ عَلَى ٱلنَّارِ يُفۡتَنُونَ

(እነርሱ) በእሳት ላይ በሚፈተኑበት ቀን ነው፡፡


ذُوقُواْ فِتۡنَتَكُمۡ هَٰذَا ٱلَّذِي كُنتُم بِهِۦ تَسۡتَعۡجِلُونَ

«መከራችሁን ቅመሱ፤ ይህ ያ በእርሱ ትቻኮሉበት የነበራችሁት ነው» (ይባላሉ)፡፡


إِنَّ ٱلۡمُتَّقِينَ فِي جَنَّـٰتٖ وَعُيُونٍ

አላህን ፈሪዎቹ በአትክልቶችና በምንጮች ውስጥ ናቸው፡፡


ءَاخِذِينَ مَآ ءَاتَىٰهُمۡ رَبُّهُمۡۚ إِنَّهُمۡ كَانُواْ قَبۡلَ ذَٰلِكَ مُحۡسِنِينَ

ያንን ጌታቸው የሰጣቸውን ተቀባዮች ኾነው፤ (በገነት ውስጥ ይኾናሉ)፡፡ እነርሱ ከዚህ በፊት መልካም ሰሪዎች ነበሩና፡፡


كَانُواْ قَلِيلٗا مِّنَ ٱلَّيۡلِ مَا يَهۡجَعُونَ

ከሌሊቱ ጥቂትን ብቻ ይተኙ ነበሩ፡፡


وَبِٱلۡأَسۡحَارِ هُمۡ يَسۡتَغۡفِرُونَ

በሌሊቱ መጨረሻዎችም እነርሱ ምሕረትን ይለምናሉ፡፡


وَفِيٓ أَمۡوَٰلِهِمۡ حَقّٞ لِّلسَّآئِلِ وَٱلۡمَحۡرُومِ

በገንዘቦቻቸውም ውስጥ ለለማኝና (ከልመና) ለተከለከለም (በችሮታቸው) መብት አልለ፡፡


وَفِي ٱلۡأَرۡضِ ءَايَٰتٞ لِّلۡمُوقِنِينَ

በምድርም ውስጥ ለሚያረጋግጡ ሰዎች ምልክቶች አልሉ፡፡


وَفِيٓ أَنفُسِكُمۡۚ أَفَلَا تُبۡصِرُونَ

በነፍሶቻችሁም ውስጥ (ምልክቶች አልሉ)፤ ታዲያ አትመለከቱምን?›



الصفحة التالية
Icon