أَفَتُمَٰرُونَهُۥ عَلَىٰ مَا يَرَىٰ

ታዲያ በሚያየው ላይ ትከራከሩታላችሁን?


وَلَقَدۡ رَءَاهُ نَزۡلَةً أُخۡرَىٰ

በሌላይቱም መውረድ ጊዜ በእርግጥ አይቶታል፡፡


عِندَ سِدۡرَةِ ٱلۡمُنتَهَىٰ

በመጨረሻይቱ ቁርቁራ አጠገብ፤


عِندَهَا جَنَّةُ ٱلۡمَأۡوَىٰٓ

እርሷ ዘንድ መኖሪያይቱ ገነት ያለች ስትኾን፡፡


إِذۡ يَغۡشَى ٱلسِّدۡرَةَ مَا يَغۡشَىٰ

ቁርቁራይቱን የሚሸፍን ነገር በሚሸፍናት ጊዜ (አየው)፡፡


مَا زَاغَ ٱلۡبَصَرُ وَمَا طَغَىٰ

ዓይኑ (ካየው) አልተዘነበለም፡፡ ወሰንም አላለፈም፡፡


لَقَدۡ رَأَىٰ مِنۡ ءَايَٰتِ رَبِّهِ ٱلۡكُبۡرَىٰٓ

ከጌታው ታምራቶች ታላላቆቹን በእርግጥ አየ፡፡


أَفَرَءَيۡتُمُ ٱللَّـٰتَ وَٱلۡعُزَّىٰ

አል-ላትንና አል-ዑዛን አያችሁን?


وَمَنَوٰةَ ٱلثَّالِثَةَ ٱلۡأُخۡرَىٰٓ

ሦስተኛይቱንም አነስተኛዋን መናትን (አያችሁን? የምትግገዟቸው ኃይል አላቸውን?)


أَلَكُمُ ٱلذَّكَرُ وَلَهُ ٱلۡأُنثَىٰ

ለእናንተ ወንድ ለእርሱም ሴት (ልጅ) ይኖራልን?


تِلۡكَ إِذٗا قِسۡمَةٞ ضِيزَىٰٓ

ይህቺ ያን ጊዜ አድላዊ ክፍያ ናት፡፡



الصفحة التالية
Icon