وَأَنَّهُۥ خَلَقَ ٱلزَّوۡجَيۡنِ ٱلذَّكَرَ وَٱلۡأُنثَىٰ

እርሱም ሁለቱን ዓይነቶች ወንድንና ሴትን ፈጠረ፡፡


مِن نُّطۡفَةٍ إِذَا تُمۡنَىٰ

ከፍትወት ጠብታ (በማህጸን ውስጥ) በምትፈሰስ ጊዜ፡፡


وَأَنَّ عَلَيۡهِ ٱلنَّشۡأَةَ ٱلۡأُخۡرَىٰ

የኋለኛይቱም ማስነሳት በእርሱ ላይ ነው፡፡


وَأَنَّهُۥ هُوَ أَغۡنَىٰ وَأَقۡنَىٰ

እነሆ እርሱም አከበረ፣ ጥሪተኛም አደረገ፡፡


وَأَنَّهُۥ هُوَ رَبُّ ٱلشِّعۡرَىٰ

እነሆ እርሱም የሺዕራ ጌታ ነው፡፡


وَأَنَّهُۥٓ أَهۡلَكَ عَادًا ٱلۡأُولَىٰ

እነሆ እርሱም የፊተኛይቱን ዓድ አጥፍቷል፡፡


وَثَمُودَاْ فَمَآ أَبۡقَىٰ

ሰሙድንም (አጥፍቷል)፤ አላስቀረምም፡፡


وَقَوۡمَ نُوحٖ مِّن قَبۡلُۖ إِنَّهُمۡ كَانُواْ هُمۡ أَظۡلَمَ وَأَطۡغَىٰ

በፊትም የኑሕን ሕዝቦች (አጥፍቷል)፡፡ እነርሱ በጣም በደለኞችና እጅግ የጠመሙ እነርሱ ነበሩና፡፡


وَٱلۡمُؤۡتَفِكَةَ أَهۡوَىٰ

የተገለበጠችውንም ከተማ ደፋ፡፡


فَغَشَّىٰهَا مَا غَشَّىٰ

ያለበሳትንም አለበሳት፡፡


فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكَ تَتَمَارَىٰ

ከጌታህም ጸጋዎች በየትኛው ትጠራጠራለህ?



الصفحة التالية
Icon