أَمۡ يَقُولُونَ نَحۡنُ جَمِيعٞ مُّنتَصِرٞ

ወይስ «እኛ የተረዳን ክምቹዎች ነን» ይላሉን?


سَيُهۡزَمُ ٱلۡجَمۡعُ وَيُوَلُّونَ ٱلدُّبُرَ

ክምቹዎቹ በእርግጥ ድል ይምመታሉ፡፡ ጀርባዎችንም ያዞራሉ፡፡


بَلِ ٱلسَّاعَةُ مَوۡعِدُهُمۡ وَٱلسَّاعَةُ أَدۡهَىٰ وَأَمَرُّ

ይልቁንም ሰዓቲቱ (ትንሣኤ) ቀጠሮዋቸው ናት፡፡ ሰዓቲቱም በጣም የከበደችና የመረረች ናት፡፡


إِنَّ ٱلۡمُجۡرِمِينَ فِي ضَلَٰلٖ وَسُعُرٖ

አመጸኞች በስህተትና በእሳቶች ውስጥ ናቸው፡፡


يَوۡمَ يُسۡحَبُونَ فِي ٱلنَّارِ عَلَىٰ وُجُوهِهِمۡ ذُوقُواْ مَسَّ سَقَرَ

በእሳት ውስጥ በፊቶቻቸው በሚጎተቱበት ቀን «የሰቀርን መንካት ቅመሱ» (ይባላሉ)፡፡


إِنَّا كُلَّ شَيۡءٍ خَلَقۡنَٰهُ بِقَدَرٖ

እኛ ሁሉን ነገር በልክ ፈጠርነው፡፡


وَمَآ أَمۡرُنَآ إِلَّا وَٰحِدَةٞ كَلَمۡحِۭ بِٱلۡبَصَرِ

ትእዛዛችንም እንደ ዓይን ቅጽበት አንዲት (ቃል) እንጅ ሌላ አይደለም፡፡


وَلَقَدۡ أَهۡلَكۡنَآ أَشۡيَاعَكُمۡ فَهَلۡ مِن مُّدَّكِرٖ

ብጤዎቻችሁንም በእርግጥ አጠፋን፡፡ ተገሳጭም አልለን?


وَكُلُّ شَيۡءٖ فَعَلُوهُ فِي ٱلزُّبُرِ

የሠሩትም ነገር ሁሉ በመጽሐፎች ውስጥ ነው፡፡


وَكُلُّ صَغِيرٖ وَكَبِيرٖ مُّسۡتَطَرٌ

ትንሹም ትልቁም ሁሉ የተጻፈ ነው፡፡



الصفحة التالية
Icon