فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ

(ሰዎችና ጋኔኖች ሆይ!) ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?


خَلَقَ ٱلۡإِنسَٰنَ مِن صَلۡصَٰلٖ كَٱلۡفَخَّارِ

ሰውን እንደ ሸክላ ከሚቅጨለጨል ደረቅ ጭቃ ፈጠረው፡፡


وَخَلَقَ ٱلۡجَآنَّ مِن مَّارِجٖ مِّن نَّارٖ

ጃንንም ከእሳት ከኾነ ነበልባል ፈጠረው፡፡


فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?


رَبُّ ٱلۡمَشۡرِقَيۡنِ وَرَبُّ ٱلۡمَغۡرِبَيۡنِ

የሁለቱ ምሥራቆች ጌታ፤ የሁለቱ ምዕራቦችም ጌታ ነው፡፡


فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?


مَرَجَ ٱلۡبَحۡرَيۡنِ يَلۡتَقِيَانِ

ሁለቱን ባሕሮች የሚገናኙ ሲኾኑ ለቀቃቸው፡፡


بَيۡنَهُمَا بَرۡزَخٞ لَّا يَبۡغِيَانِ

(እንዳይዋሐዱ) በመካከላቸው ጋራጅ አልለ፡፡ (አንዱ ባንዱ ላይ) ወሰን አያልፉም፡፡


فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታሰተባብላላችሁ?›


يَخۡرُجُ مِنۡهُمَا ٱللُّؤۡلُؤُ وَٱلۡمَرۡجَانُ

ሉልና መርጃን ከሁለቱ ይወጣል፡፡



الصفحة التالية
Icon