فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?


مُتَّكِـِٔينَ عَلَىٰ فُرُشِۭ بَطَآئِنُهَا مِنۡ إِسۡتَبۡرَقٖۚ وَجَنَى ٱلۡجَنَّتَيۡنِ دَانٖ

የውስጥ ጉስጉሳቸው ከወፍራም ሐር በኾኑ ምንጣፎች ላይ የተመቻቹ ሲኾኑ (ይንፈላሰሳሉ)፡፡ የሁለቱም ገነቶች ፍሬ (ለለቃሚ) ቅርብ ነው፡፡


فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?


فِيهِنَّ قَٰصِرَٰتُ ٱلطَّرۡفِ لَمۡ يَطۡمِثۡهُنَّ إِنسٞ قَبۡلَهُمۡ وَلَا جَآنّٞ

በውስጣቸው ከበፊታቸው (ከባሎቻቸው በፊት) ሰውም ጃንም ያልገሰሳቸው ዓይኖቻቸውን (በባሎቻቸው ላይ) አሳጣሪዎች (ሴቶች) አልሉ፡፡


فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?


كَأَنَّهُنَّ ٱلۡيَاقُوتُ وَٱلۡمَرۡجَانُ

ልክ ያቁትና መርጃን ይመስላሉ፡፡


فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ

ከጌታችሁም ጸጋዎቸ በየትኛው ታስተባብላላችሁ?


هَلۡ جَزَآءُ ٱلۡإِحۡسَٰنِ إِلَّا ٱلۡإِحۡسَٰنُ

የበጎ ሥራ ዋጋ በጎ እንጅ ሌላ ነውን?


فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?



الصفحة التالية
Icon