وَكَانُواْ يَقُولُونَ أَئِذَا مِتۡنَا وَكُنَّا تُرَابٗا وَعِظَٰمًا أَءِنَّا لَمَبۡعُوثُونَ

ይሉም ነበሩ፡- «በሞትንና ዐፈር፣ ዐጥንቶችም በኾን ጊዜ እኛ በእርግጥ የምንቀሰቀስ ነን?


أَوَءَابَآؤُنَا ٱلۡأَوَّلُونَ

«የፊተኞቹ አባቶቻችንም?»


قُلۡ إِنَّ ٱلۡأَوَّلِينَ وَٱلۡأٓخِرِينَ

በላቸው፡- «ፊተኞቹም ኋለኞቹም፡፡


لَمَجۡمُوعُونَ إِلَىٰ مِيقَٰتِ يَوۡمٖ مَّعۡلُومٖ

«በተወሰነ ቀን ቀጠሮ በእርግጥ ተሰብሳቢዎች ናቸው፡፡


ثُمَّ إِنَّكُمۡ أَيُّهَا ٱلضَّآلُّونَ ٱلۡمُكَذِّبُونَ

«ከዚያም እናንተ ጠማሞች አስተባባዮች ሆይ!


لَأٓكِلُونَ مِن شَجَرٖ مِّن زَقُّومٖ

« ከዘቁም ዛፍ በእርግጥ በይዎች ናችሁ፡፡


فَمَالِـُٔونَ مِنۡهَا ٱلۡبُطُونَ

«ከእርሷም ሆዶቻችሁን ሞይዎች ናችሁ፡፡


فَشَٰرِبُونَ عَلَيۡهِ مِنَ ٱلۡحَمِيمِ

«በእርሱ ላይም ከፈላ ውሃ ጠጪዎች ናችሁ፡፡


فَشَٰرِبُونَ شُرۡبَ ٱلۡهِيمِ

«የተጠሙንም ግመሎች አጠጣጥ ብጤ ጠጪዎች ናችሁ፡፡»


هَٰذَا نُزُلُهُمۡ يَوۡمَ ٱلدِّينِ

ይህ በፍርዱ ቀን መስተንግዷቸው ነው፡፡


نَحۡنُ خَلَقۡنَٰكُمۡ فَلَوۡلَا تُصَدِّقُونَ

እኛ ፈጠርናችሁ አታምኑምን?



الصفحة التالية
Icon