مَّنَّاعٖ لِّلۡخَيۡرِ مُعۡتَدٍ أَثِيمٍ

ለበጎ ነገር በጣም ከልካይን፣ ወሰን አላፊን፣ ኃጢአተኛን፤


عُتُلِّۭ بَعۡدَ ذَٰلِكَ زَنِيمٍ

ልበ ደረቅን፣ ከዚህ በኋላ ዲቃላን (ሁሉ አትታዘዝ)፡፡


أَن كَانَ ذَا مَالٖ وَبَنِينَ

የገንዘብና የልጆች ባለቤት በመኾኑ (ያስተባብላል)፡፡


إِذَا تُتۡلَىٰ عَلَيۡهِ ءَايَٰتُنَا قَالَ أَسَٰطِيرُ ٱلۡأَوَّلِينَ

በእርሱ ላይ አንቀጾቻችን በሚነበቡ ጊዜ «የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ተረቶች ናቸው» ይላል፡፡


سَنَسِمُهُۥ عَلَى ٱلۡخُرۡطُومِ

በአፍንጫው ላይ በእርግጥ (የሚነወርበት) ምልክት እናደርግበታለን፡፡


إِنَّا بَلَوۡنَٰهُمۡ كَمَا بَلَوۡنَآ أَصۡحَٰبَ ٱلۡجَنَّةِ إِذۡ أَقۡسَمُواْ لَيَصۡرِمُنَّهَا مُصۡبِحِينَ

እኛ የአትክልቲቱን ባለቤቶቸ እንደ ሞከርን (የመካን ሰዎች) ሞከርናቸው፡፡ ማልደው (ፍሬዋን) ሊለቅሟት በማሉ ጊዜ፡፡


وَلَا يَسۡتَثۡنُونَ

(በመሓላቸው) አያስቀሩምም፡፡


فَطَافَ عَلَيۡهَا طَآئِفٞ مِّن رَّبِّكَ وَهُمۡ نَآئِمُونَ

እነርሱ የተኙ ኾነውም ሳሉ ከጌታህ የኾነ ዟሪ በእርሷ ላይ ዞረባት፡፡


فَأَصۡبَحَتۡ كَٱلصَّرِيمِ

እንደ ሌሊት ጨለማም ኾና አነጋች፤ (ከሰለች)፡፡


فَتَنَادَوۡاْ مُصۡبِحِينَ

ያነጉም ኾነው ተጠራሩ፡፡



الصفحة التالية
Icon