إِلَّا ٱلۡمُصَلِّينَ

ሰጋጆቹ ብቻ ሲቀሩ፡፡


ٱلَّذِينَ هُمۡ عَلَىٰ صَلَاتِهِمۡ دَآئِمُونَ

እነዚያ እነርሱ በስግደታቸው ላይ ዘውታሪዎች የኾኑት፡፡


وَٱلَّذِينَ فِيٓ أَمۡوَٰلِهِمۡ حَقّٞ مَّعۡلُومٞ

እነዚያም በገንዘቦቻቸው ላይ የታወቀ መብት ያለባቸው የኾኑት፡፡


لِّلسَّآئِلِ وَٱلۡمَحۡرُومِ

ለለማኝ ከልመና ለሚከለከልም (መብት ያለባቸው የኾኑት)፡፡


وَٱلَّذِينَ يُصَدِّقُونَ بِيَوۡمِ ٱلدِّينِ

እነዚያም በፍርዱ ቀን እውነት የሚሉት (የሚያረጋግጡት)፡፡


وَٱلَّذِينَ هُم مِّنۡ عَذَابِ رَبِّهِم مُّشۡفِقُونَ

እነዚያም እነርሱ ከጌታቸው ቅጣት ፈሪዎች የኾኑት፡፡


إِنَّ عَذَابَ رَبِّهِمۡ غَيۡرُ مَأۡمُونٖ

የጌታቸው ቅጣት (መምጣቱ) የማያስተማምን ነውና፡፡


وَٱلَّذِينَ هُمۡ لِفُرُوجِهِمۡ حَٰفِظُونَ

እነዚያም እነርሱ ብልቶቻቸውን ጠባቂዎች የኾኑት፡፡


إِلَّا عَلَىٰٓ أَزۡوَٰجِهِمۡ أَوۡ مَا مَلَكَتۡ أَيۡمَٰنُهُمۡ فَإِنَّهُمۡ غَيۡرُ مَلُومِينَ

በሚስቶቻቸው ወይም እጆቻቸው በያዙዋቸው (ባሪያዎች) ላይ ሲቀር፡፡ እነርሱ (በእነዚህ) የማይወቀሱ ናቸውና፡፡


فَمَنِ ٱبۡتَغَىٰ وَرَآءَ ذَٰلِكَ فَأُوْلَـٰٓئِكَ هُمُ ٱلۡعَادُونَ

ከዚያም ወዲያ የፈለገ ሰው እነዚያ እነሱ ድንበር አላፊዎች ናቸው፡፡



الصفحة التالية
Icon