وَبَنِينَ شُهُودٗا

(በያደባባዩ) ተገኝዎች የኾኑ ወንዶች ልጆችንም፡፡


وَمَهَّدتُّ لَهُۥ تَمۡهِيدٗا

ለእርሱም (ኑሮውን) መዘርጋትን የዘረጋሁለት (ከኾነ ሰው ገር ተዎኝ)፡፡


ثُمَّ يَطۡمَعُ أَنۡ أَزِيدَ

ከዚያም ልጨምርለት ይከጅላል፡፡


كَلَّآۖ إِنَّهُۥ كَانَ لِأٓيَٰتِنَا عَنِيدٗا

ይከልከል፤ እርሱ ለአንቀጾቻችን በእርግጥ ተቃዋሚ ነበር፡፡


سَأُرۡهِقُهُۥ صَعُودًا

በእርግጥ ችግርን አስገድደዋለሁ፡፡


إِنَّهُۥ فَكَّرَ وَقَدَّرَ

እርሱ (በቁርኣን ነገር) ሐሰበ፤ ገመተም፡፡


فَقُتِلَ كَيۡفَ قَدَّرَ

ተረገመም፤ እንዴት ገመተ!


ثُمَّ قُتِلَ كَيۡفَ قَدَّرَ

ከዚያም (ከሞት በኋላ) ተረገመ፡፡ እንዴት ገመተ!


ثُمَّ نَظَرَ

ከዚያም እንደ ገና (በቁርኣኑ ነገር) ተመለከተ፡፡


ثُمَّ عَبَسَ وَبَسَرَ

ከዚያም ፊቱን አጨፈገገ፤ አኮማተረም፡፡


ثُمَّ أَدۡبَرَ وَٱسۡتَكۡبَرَ

ከዚያም (ከማመን) ዞረ፤ ኮራም፡፡


فَقَالَ إِنۡ هَٰذَآ إِلَّا سِحۡرٞ يُؤۡثَرُ

አለም «ይህ (ከሌላ) የሚቀዳ ድግምት እንጅ ሌላ አይደለም፡፡



الصفحة التالية
Icon