أَلَمۡ نَجۡعَلِ ٱلۡأَرۡضَ كِفَاتًا

ምድርን ሰብሳቢ አላደረግናትምን?


أَحۡيَآءٗ وَأَمۡوَٰتٗا

ሕያዋን ኾናችሁ ሙታንም ኾናችሁ፡፡


وَجَعَلۡنَا فِيهَا رَوَٰسِيَ شَٰمِخَٰتٖ وَأَسۡقَيۡنَٰكُم مَّآءٗ فُرَاتٗا

በውስጧም ከፍተኛዎችን ተራራዎች አደረግን፡፡ ጣፋጭ ውሃንም አጠጣናችሁ፡፡


وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡


ٱنطَلِقُوٓاْ إِلَىٰ مَا كُنتُم بِهِۦ تُكَذِّبُونَ

«ወደዚያ በእርሱ ታስተባብሉ ወደ ነበራችሁት (ቅጣት) አዝግሙ፡፡


ٱنطَلِقُوٓاْ إِلَىٰ ظِلّٖ ذِي ثَلَٰثِ شُعَبٖ

«ባለ ሦስት ቅርንጫፎች ወደ ኾነው ጥላ አዝግሙ፤» (ይባላሉ)፡፡


لَّا ظَلِيلٖ وَلَا يُغۡنِي مِنَ ٱللَّهَبِ

አጠላይ ያልኾነ ከእሳቱም ላንቃ የማያድን ወደ ኾነው (አዝግሙ)፡፡


إِنَّهَا تَرۡمِي بِشَرَرٖ كَٱلۡقَصۡرِ

እርሷ እንደ ታላላቅ ሕንጻ የኾኑን ቃንቄዎች ትወረውራለች፡፡


كَأَنَّهُۥ جِمَٰلَتٞ صُفۡرٞ

(ቃንቄውም) ልክ ዳለቻዎች ግመሎችን ይመስላል፡፡


وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡


هَٰذَا يَوۡمُ لَا يَنطِقُونَ

ይህ የማይናገሩበት ቀን ነው፡፡



الصفحة التالية
Icon