وَجَعَلۡنَا سِرَاجٗا وَهَّاجٗا

አንጸባራቂ ብርሃንንም አደረግን፡፡


وَأَنزَلۡنَا مِنَ ٱلۡمُعۡصِرَٰتِ مَآءٗ ثَجَّاجٗا

ከአረገዙት ደመናዎችም ተንቧቢ ውሃን አወረድን፡፡


لِّنُخۡرِجَ بِهِۦ حَبّٗا وَنَبَاتٗا

በእርሱ እኽልንና ቅጠላ ቅጠልን እናወጣ ዘንድ (አወረድን)፡፡


وَجَنَّـٰتٍ أَلۡفَافًا

የተቆላለፉ አትክልቶችንም፡፡


إِنَّ يَوۡمَ ٱلۡفَصۡلِ كَانَ مِيقَٰتٗا

የመለያው ቀን የተወሰነ ጊዜ ነው፡፡


يَوۡمَ يُنفَخُ فِي ٱلصُّورِ فَتَأۡتُونَ أَفۡوَاجٗا

በቀንዱ በሚነፋና የተለያዩ ጭፍሮች ኾናችሁ በምትመጡ ቀን ነው፡፡


وَفُتِحَتِ ٱلسَّمَآءُ فَكَانَتۡ أَبۡوَٰبٗا

ሰማይም በምትከፈትና (ባለ) ደጃፎችም በምትኾንበት፡፡


وَسُيِّرَتِ ٱلۡجِبَالُ فَكَانَتۡ سَرَابًا

ጋራዎችም በሚነዱበት (እንደ) ሲሪብዱም በሚኾኑበት (ቀን) ነው፡፡


إِنَّ جَهَنَّمَ كَانَتۡ مِرۡصَادٗا

ገሀነም መጠባበቂያ (ስፍራ) ናት፡፡


لِّلطَّـٰغِينَ مَـَٔابٗا

ለሕግ ተላላፊዎች መመለሻ ስትኾን፡፡


لَّـٰبِثِينَ فِيهَآ أَحۡقَابٗا

በውስጧ ብዙን ዘመናት ነዋሪዎች ሲኾኑ፤



الصفحة التالية
Icon