وَبُرِّزَتِ ٱلۡجَحِيمُ لِمَن يَرَىٰ

ገሀነምም ለሚያይ ሰው በተገለጠች ጊዜ፣


فَأَمَّا مَن طَغَىٰ

የካደ ሰውማ፣


وَءَاثَرَ ٱلۡحَيَوٰةَ ٱلدُّنۡيَا

ቅርቢቱንም ሕይወት የመረጠ፣


فَإِنَّ ٱلۡجَحِيمَ هِيَ ٱلۡمَأۡوَىٰ

ገሀነም እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡


وَأَمَّا مَنۡ خَافَ مَقَامَ رَبِّهِۦ وَنَهَى ٱلنَّفۡسَ عَنِ ٱلۡهَوَىٰ

በጌታው ፊት መቆምን የፈራ ሰውማ ነፍሱንም ከዝንባሌዋ የከለከለ


فَإِنَّ ٱلۡجَنَّةَ هِيَ ٱلۡمَأۡوَىٰ

ገነት እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡


يَسۡـَٔلُونَكَ عَنِ ٱلسَّاعَةِ أَيَّانَ مُرۡسَىٰهَا

«ከሰዓቲቱ መቼ ነው መኾኛዋ?» ሲሉ ይጠይቁሃል፡፡


فِيمَ أَنتَ مِن ذِكۡرَىٰهَآ

አንተ እርሷን ከማስታወስ በምን ውስጥ ነህ?


إِلَىٰ رَبِّكَ مُنتَهَىٰهَآ

(የዕውቀት) መጨረሻዋ ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡


إِنَّمَآ أَنتَ مُنذِرُ مَن يَخۡشَىٰهَا

አንተ የሚፈራትን ሰው አስፈራሪ ብቻ ነህ፡፡


كَأَنَّهُمۡ يَوۡمَ يَرَوۡنَهَا لَمۡ يَلۡبَثُوٓاْ إِلَّا عَشِيَّةً أَوۡ ضُحَىٰهَا

እነርሱ በሚያዩዋት ቀን ያንዲት ቀን ምሽትን ወይም ረፏዷን እንጅ ያልቆዩ ይመስላሉ፡፡



الصفحة التالية
Icon