أَنَّا صَبَبۡنَا ٱلۡمَآءَ صَبّٗا

እኛ ውሃን ማንቧቧትን ያንቧቧን መኾናችንን፡፡


ثُمَّ شَقَقۡنَا ٱلۡأَرۡضَ شَقّٗا

ከዚያም ምድርን (በደካማ ቡቃያ) መሰንጠቅን የሰነጠቅን፤


فَأَنۢبَتۡنَا فِيهَا حَبّٗا

በውስጧም እኽልን ያበቀልን፤


وَعِنَبٗا وَقَضۡبٗا

ወይንንም፤ እርጥብ ያበቀልን፤


وَزَيۡتُونٗا وَنَخۡلٗا

የዘይት ወይራንም ዘንባባንም፤


وَحَدَآئِقَ غُلۡبٗا

ጭፍቆች አትክልቶችንም፤


وَفَٰكِهَةٗ وَأَبّٗا

ፍራፍሬንም ገለባንም፤ (ያበቀልን መኾናችንን ይመልከት)፡፡


مَّتَٰعٗا لَّكُمۡ وَلِأَنۡعَٰمِكُمۡ

ለእናንተም ለእንስሶቻችሁም መጠቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን ሠራን)፡፡


فَإِذَا جَآءَتِ ٱلصَّآخَّةُ

አደንቋሪይቱም (መከራ) በመጣች ጊዜ፤


يَوۡمَ يَفِرُّ ٱلۡمَرۡءُ مِنۡ أَخِيهِ

ሰው ከወንድሙ በሚሸሽበት ቀን፤


وَأُمِّهِۦ وَأَبِيهِ

ከናቱም ካባቱም፤


وَصَٰحِبَتِهِۦ وَبَنِيهِ

ከሚስቱም ከልጁም፤



الصفحة التالية
Icon