وَٱلطُّورِ

በጡር (ጋራ) እምላለሁ፡፡


وَكِتَٰبٖ مَّسۡطُورٖ

በተጻፈው መጽሐፍም፡፡


فِي رَقّٖ مَّنشُورٖ

በተዘረጋ ብራና ላይ፤ (በተጻፈው)፡፡


وَٱلۡبَيۡتِ ٱلۡمَعۡمُورِ

በደመቀው ቤትም፡፡


وَٱلسَّقۡفِ ٱلۡمَرۡفُوعِ

ከፍ በተደረገው ጣራም፡፡


وَٱلۡبَحۡرِ ٱلۡمَسۡجُورِ

በተመላው ባሕርም እምላለሁ፡፡


إِنَّ عَذَابَ رَبِّكَ لَوَٰقِعٞ

የጌታህ ቅጣት በእርግጥ ወዳቂ ነው፤ (የማይቀር ነው)፡፡


مَّا لَهُۥ مِن دَافِعٖ

ለእርሱ ምንም ገፍታሪ የለውም፡፡


يَوۡمَ تَمُورُ ٱلسَّمَآءُ مَوۡرٗا

ሰማይ ብርቱ መዞርን በምትዞርበት ቀን (ይኾናል)፡፡


وَتَسِيرُ ٱلۡجِبَالُ سَيۡرٗا

ተራራዎችም መኼድን በሚኼዱበት (ቀን)፡፡


فَوَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ

ለአስተባባዮችም ያን ጊዜ ወዮላቸው፡፡


ٱلَّذِينَ هُمۡ فِي خَوۡضٖ يَلۡعَبُونَ

ለእነዚያ እነርሱ በውሸት ውስጥ የሚጫወቱ ለኾኑት፡፡



الصفحة التالية
Icon