وَيۡلٞ لِّلۡمُطَفِّفِينَ

ለሰላቢዎች ወዮላቸው፡፡


ٱلَّذِينَ إِذَا ٱكۡتَالُواْ عَلَى ٱلنَّاسِ يَسۡتَوۡفُونَ

ለእነዚያ ከሰዎች ባስሰፈሩ ጊዜ የሚያስሞሉ፡፡


وَإِذَا كَالُوهُمۡ أَو وَّزَنُوهُمۡ يُخۡسِرُونَ

ለእነርሱም (ለሰዎቹ) በሰፈሩ ወይም በመዘኑላቸው ጊዜ የሚያጎድሉ (ለኾኑት)፡፡


أَلَا يَظُنُّ أُوْلَـٰٓئِكَ أَنَّهُم مَّبۡعُوثُونَ

እነዚያ እነርሱ ተቀስቃሾች መኾናቸውን አያውቁምን?


لِيَوۡمٍ عَظِيمٖ

በታላቁ ቀን፡፡


يَوۡمَ يَقُومُ ٱلنَّاسُ لِرَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ

ሰዎች ሁሉ ለዓለማት ጌታ (ፍርድ)፤ በሚቆሙበት ቀን (ተቀስቃሾች መኾናቸውን)፡፡


كَلَّآ إِنَّ كِتَٰبَ ٱلۡفُجَّارِ لَفِي سِجِّينٖ

በእውነት የከሓዲዎቹ (የሰላቢዎቹ) መጽሐፍ በእርግጥ በሲጂን ውስጥ ነው፡፡


وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا سِجِّينٞ

ሲጂንም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ?


كِتَٰبٞ مَّرۡقُومٞ

የታተመ መጽሐፍ ነው፡፡


وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡


ٱلَّذِينَ يُكَذِّبُونَ بِيَوۡمِ ٱلدِّينِ

ለእነዚያ በፍርዱ ቀን ለሚያስተባብሉት፡፡



الصفحة التالية
Icon