وَٱلشَّمۡسِ وَضُحَىٰهَا

በፀሐይና በብርሃኗ እምላለሁ፡፡


وَٱلۡقَمَرِ إِذَا تَلَىٰهَا

በጨረቃም በተከተላት ጊዜ፤


وَٱلنَّهَارِ إِذَا جَلَّىٰهَا

በቀኑም (ፀሐይን) በገለጻት ጊዜ፤


وَٱلَّيۡلِ إِذَا يَغۡشَىٰهَا

በሌሊቱም በሸፈናት ጊዜ፤


وَٱلسَّمَآءِ وَمَا بَنَىٰهَا

በሰማይቱም በገነባትም (ጌታ)፤


وَٱلۡأَرۡضِ وَمَا طَحَىٰهَا

በምድሪቱም በዘረጋትም፤


وَنَفۡسٖ وَمَا سَوَّىٰهَا

በነፍስም ባስተካከላትም፤


فَأَلۡهَمَهَا فُجُورَهَا وَتَقۡوَىٰهَا

አመጽዋንና ፍርሃትዋንም ባሳወቃት (አምላክ እምላለሁ)፡፡


قَدۡ أَفۡلَحَ مَن زَكَّىٰهَا

(ከኀጢኣት) ያጠራት ሰው ፍላጎቱን በእርግጥ አገኘ፡፡


وَقَدۡ خَابَ مَن دَسَّىٰهَا

(በኀጢኣት) የሸፈናትም ሰው በእውነት አፈረ፡፡


كَذَّبَتۡ ثَمُودُ بِطَغۡوَىٰهَآ

ሠሙድ ወሰን በማለፍዋ አስተባበለች፡፡


إِذِ ٱنۢبَعَثَ أَشۡقَىٰهَا

ጠማማዋ በተንቀሳቀሰ ጊዜ፡፡



الصفحة التالية
Icon