أَرَءَيۡتَ ٱلَّذِي يُكَذِّبُ بِٱلدِّينِ

ያንን በምርመራው የሚያስተባብለውን አየህን? (ዐወቅከውን?)


فَذَٰلِكَ ٱلَّذِي يَدُعُّ ٱلۡيَتِيمَ

ይህም ያ የቲምን በኀይል የሚገፈትረው፤


وَلَا يَحُضُّ عَلَىٰ طَعَامِ ٱلۡمِسۡكِينِ

ድኻንም በማብላት ላይ የማያግባባው ሰው ነው፡፡


فَوَيۡلٞ لِّلۡمُصَلِّينَ

ወዮላቸው ለሰጋጆች፡፡


ٱلَّذِينَ هُمۡ عَن صَلَاتِهِمۡ سَاهُونَ

ለእነዚያ እነርሱ ከስግደታቸው ዘንጊዎች ለኾኑት፤ (ሰጋጆች)፡፡


ٱلَّذِينَ هُمۡ يُرَآءُونَ

ለእነዚያ እነርሱ ይዩልኝ ባዮች ለኾኑት፡፡


وَيَمۡنَعُونَ ٱلۡمَاعُونَ

የዕቃ ትውስትንም (ሰዎችን) የሚከለክሉ ለኾኑት (ወዮላቸው)፡፡



الصفحة التالية
Icon