فَسَوۡفَ يَدۡعُواْ ثُبُورٗا

(ዋ! ጥፋቴ በማለት) ጥፋትን በእርግጥ ይጠራል፡፡


وَيَصۡلَىٰ سَعِيرًا

የተጋጋመች እሳትንም ይገባል፡፡


إِنَّهُۥ كَانَ فِيٓ أَهۡلِهِۦ مَسۡرُورًا

እርሱ በቤተሰቡ ውስጥ ተደሳች ነበርና፡፡


إِنَّهُۥ ظَنَّ أَن لَّن يَحُورَ

እርሱ (ወደ አላህ) የማይመለስ መኾኑን አስቧልና፡፡


بَلَىٰٓۚ إِنَّ رَبَّهُۥ كَانَ بِهِۦ بَصِيرٗا

አይደለም (ይመለሳል)፡፡ ጌታው በእርሱ (መመለስ) ዐዋቂ ነበር፤ (ነውም)፡፡


فَلَآ أُقۡسِمُ بِٱلشَّفَقِ

አትካዱ፤ በወጋገኑ እምላለሁ፡፡


وَٱلَّيۡلِ وَمَا وَسَقَ

በሌሊቱም በሰበሰውም ሁሉ፤


وَٱلۡقَمَرِ إِذَا ٱتَّسَقَ

በጨረቃውም በሞላ ጊዜ (እምላለሁ)፡፡


لَتَرۡكَبُنَّ طَبَقًا عَن طَبَقٖ

ከኹነታ በኋላ ወደ ሌላ ኹነታ ትለዋወጣላችሁ፡፡


فَمَا لَهُمۡ لَا يُؤۡمِنُونَ

የማያምኑት ለእነርሱ ምን አላቸው?


وَإِذَا قُرِئَ عَلَيۡهِمُ ٱلۡقُرۡءَانُ لَا يَسۡجُدُونَۤ۩

በእነርሱም ላይ ቁርኣን በተነበበ ጊዜ የማይሰግዱት፤ (ምንአላቸው?)



الصفحة التالية
Icon