فَصَبَّ عَلَيۡهِمۡ رَبُّكَ سَوۡطَ عَذَابٍ

በእነርሱ ላይም ጌታህ የቅጣትን አለንጋ አወረደባቸው፡፡


إِنَّ رَبَّكَ لَبِٱلۡمِرۡصَادِ

ጌታህ በመጠባበቂያ ላይ ነውና፡፡


فَأَمَّا ٱلۡإِنسَٰنُ إِذَا مَا ٱبۡتَلَىٰهُ رَبُّهُۥ فَأَكۡرَمَهُۥ وَنَعَّمَهُۥ فَيَقُولُ رَبِّيٓ أَكۡرَمَنِ

ሰውማ ጌታው በሞከረው ጊዜ፣ ባከበረውና ባጣቀመውም (ጊዜ) «ጌታዬ አከበረኝ (አበለጠኝ)» ይላል፡፡


وَأَمَّآ إِذَا مَا ٱبۡتَلَىٰهُ فَقَدَرَ عَلَيۡهِ رِزۡقَهُۥ فَيَقُولُ رَبِّيٓ أَهَٰنَنِ

በሞከረውና በእርሱ ላይ ሲሳዩን ባጠበበ ጊዜማ «ጌታዬ አሳነሰኝ» ይላል፡፡


كَلَّاۖ بَل لَّا تُكۡرِمُونَ ٱلۡيَتِيمَ

ይከልከል፤ ይልቁንም የቲምን አታከብሩም፡፡


وَلَا تَحَـٰٓضُّونَ عَلَىٰ طَعَامِ ٱلۡمِسۡكِينِ

ድኻንም በማብላት ላይ አትታዘዙም፡፡


وَتَأۡكُلُونَ ٱلتُّرَاثَ أَكۡلٗا لَّمّٗا

የውርስንም ገንዘብ የመሰብሰብን አበላል ትበላላችሁ፡፡


وَتُحِبُّونَ ٱلۡمَالَ حُبّٗا جَمّٗا

ገንዘብንም ብዙን መውደድ ትወዳላችሁ፡፡


كَلَّآۖ إِذَا دُكَّتِ ٱلۡأَرۡضُ دَكّٗا دَكّٗا

ተዉ፤ ምድር ደጋግማ በተሰባበረች ጊዜ፤


وَجَآءَ رَبُّكَ وَٱلۡمَلَكُ صَفّٗا صَفّٗا

መላእክትም ሰልፍ ሰልፍ ኾነው ጌታህ (ትዕዛዙ) በመጣ ጊዜ፤



الصفحة التالية
Icon