قَالَ هَلۡ يَسۡمَعُونَكُمۡ إِذۡ تَدۡعُونَ

(እርሱም) አለ «በጠራችኋቸው ጊዜ ይሰሟችኋልን


أَوۡ يَنفَعُونَكُمۡ أَوۡ يَضُرُّونَ

«ወይስ ይጠቅሟችኋልን ወይስ ይጎዷችኋልን»


قَالُواْ بَلۡ وَجَدۡنَآ ءَابَآءَنَا كَذَٰلِكَ يَفۡعَلُونَ

«የለም! አባቶቻችን እንደዚሁ ሲሠሩ አገኘን» አሉት፡፡


قَالَ أَفَرَءَيۡتُم مَّا كُنتُمۡ تَعۡبُدُونَ

«ትግገዙት የነበራችሁትን አስተዋላችሁን


أَنتُمۡ وَءَابَآؤُكُمُ ٱلۡأَقۡدَمُونَ

«እናንተም የቀድሞዎቹ አባቶቻችሁም (የተግገዛችሁትን)፡፡»


فَإِنَّهُمۡ عَدُوّٞ لِّيٓ إِلَّا رَبَّ ٱلۡعَٰلَمِينَ

«እነሱም (ጣዖቶቹ) ለእኔ ጠላቶች ናቸው፡፡ ግን የዓለማት ጌታ ሲቀር (እርሱ ወዳጄ ነው)፡፡


ٱلَّذِي خَلَقَنِي فَهُوَ يَهۡدِينِ

«(እርሱ) ያ የፈጠረኝ ነው፡፡ እርሱም ይመራኛል፡፡


وَٱلَّذِي هُوَ يُطۡعِمُنِي وَيَسۡقِينِ

«ያም እርሱ የሚያበላኝና የሚያጠጣኝ ነው፡፡


وَإِذَا مَرِضۡتُ فَهُوَ يَشۡفِينِ

«በታመምኩም ጊዜ እርሱ ያሽረኛል፡፡


وَٱلَّذِي يُمِيتُنِي ثُمَّ يُحۡيِينِ

«ያም የሚገድለኝ ከዚያም ሕያው የሚያደርገኝ ነው፡፡


وَٱلَّذِيٓ أَطۡمَعُ أَن يَغۡفِرَ لِي خَطِيٓـَٔتِي يَوۡمَ ٱلدِّينِ

ያም በፍርዱ ቀን ኀጢአቴን ለእኔ ሊምር የምከጅለው ነው፡፡



الصفحة التالية
Icon