رَبِّ هَبۡ لِي حُكۡمٗا وَأَلۡحِقۡنِي بِٱلصَّـٰلِحِينَ

ጌታዬ ሆይ! ዕውቀትን ስጠኝ! በደጋጎቹም ሰዎች አስጠጋኝ፡፡


وَٱجۡعَل لِّي لِسَانَ صِدۡقٖ فِي ٱلۡأٓخِرِينَ

በኋለኞቹም ሕዝቦች ውስጥ ለእኔ መልካም ዝናን አድርግልኝ፡፡


وَٱجۡعَلۡنِي مِن وَرَثَةِ جَنَّةِ ٱلنَّعِيمِ

የጸጋይቱን ገነት ከሚወርሱትም አድርገኝ፡፡


وَٱغۡفِرۡ لِأَبِيٓ إِنَّهُۥ كَانَ مِنَ ٱلضَّآلِّينَ

ለአባቴም ማር፡፡ እርሱ ከተሳሳቱት ነበረና፡፡


وَلَا تُخۡزِنِي يَوۡمَ يُبۡعَثُونَ

በሚቀሰቀሱበት ቀንም አታዋርደኝ፡፡


يَوۡمَ لَا يَنفَعُ مَالٞ وَلَا بَنُونَ

ገንዘብም ልጆችም በማይጠቅሙበት ቀን፡፡


إِلَّا مَنۡ أَتَى ٱللَّهَ بِقَلۡبٖ سَلِيمٖ

ወደ አላህ በንጹህ ልብ የመጣ ሰው ቢኾን እንጅ፡፡»


وَأُزۡلِفَتِ ٱلۡجَنَّةُ لِلۡمُتَّقِينَ

ገነትም ለፈሪዎች በምትቀረብበት (ቀን)፡፡


وَبُرِّزَتِ ٱلۡجَحِيمُ لِلۡغَاوِينَ

ገሀነምም ለጠመሞች በምትገለጽበት (ቀን)፡፡


وَقِيلَ لَهُمۡ أَيۡنَ مَا كُنتُمۡ تَعۡبُدُونَ

ለእነሱም በሚባል ቀን «ትግገዟቸው የነበራችሁት የት ናቸው»


مِن دُونِ ٱللَّهِ هَلۡ يَنصُرُونَكُمۡ أَوۡ يَنتَصِرُونَ

«ከአላህ ሌላ ሲኾኑ ይረዱዋችኋልን ወይስ (ለራሳቸው) ይርረዳሉን»



الصفحة التالية
Icon