فَيَقُولُواْ هَلۡ نَحۡنُ مُنظَرُونَ

(በመጣባቸው ጊዜ) «እኛ የምንቆይ ነን» እስከሚሉም (አያምኑም)፡፡


أَفَبِعَذَابِنَا يَسۡتَعۡجِلُونَ

በቅጣታችን ያቻኩላሉን


أَفَرَءَيۡتَ إِن مَّتَّعۡنَٰهُمۡ سِنِينَ

አየህን ብዙ ዓመታትን ብናጣቅማቸው፤


ثُمَّ جَآءَهُم مَّا كَانُواْ يُوعَدُونَ

ከዚያም ያ ይስፈራሩበት የነበሩት ቢመጣባቸው፤


مَآ أَغۡنَىٰ عَنۡهُم مَّا كَانُواْ يُمَتَّعُونَ

ይጣቀሙበት የነበሩት ሁሉ ከእነሱ ምንም አያብቃቃቸውም፡፡


وَمَآ أَهۡلَكۡنَا مِن قَرۡيَةٍ إِلَّا لَهَا مُنذِرُونَ

አንዲትንም ከተማ ለእርሷ አስፈራሪዎች ያሏት (እና ያስተባበለች) ኾና እንጅ አላጠፋንም፡፡


ذِكۡرَىٰ وَمَا كُنَّا ظَٰلِمِينَ

(ይህች) ግሳፄ ናት፡፡ በዳዮችም አልነበርንም፡፡


وَمَا تَنَزَّلَتۡ بِهِ ٱلشَّيَٰطِينُ

ሰይጣናትም እርሱን (ቁርኣንን) አላወረዱትም፡፡


وَمَا يَنۢبَغِي لَهُمۡ وَمَا يَسۡتَطِيعُونَ

ለእነርሱም አይገባቸውም፤ አይችሉምም፡፡


إِنَّهُمۡ عَنِ ٱلسَّمۡعِ لَمَعۡزُولُونَ

እነርሱ (የመላእክትን ንግግር) ከመስማት ተከለከሉ ናቸው፡፡


فَلَا تَدۡعُ مَعَ ٱللَّهِ إِلَٰهًا ءَاخَرَ فَتَكُونَ مِنَ ٱلۡمُعَذَّبِينَ

ከአላህም ጋር ሌላን አምላክ አትግገዛ፤ ከሚቀጡት ትኾናለህና፡፡



الصفحة التالية
Icon