وَمَا تُجۡزَوۡنَ إِلَّا مَا كُنتُمۡ تَعۡمَلُونَ

ትሠሩትም የነበራችሁትን እንጂ ሌላን አትመነዱም፡፡


إِلَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلۡمُخۡلَصِينَ

ግን ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች (ቅጣትን አይቀምሱም)፡፡


أُوْلَـٰٓئِكَ لَهُمۡ رِزۡقٞ مَّعۡلُومٞ

እነዚያ ለእነርሱ የታወቀ ሲሳይ አላቸው፡፡


فَوَٰكِهُ وَهُم مُّكۡرَمُونَ

ፍራፍሬዎች (አሏቸው) እነርሱም የተከበሩ ናቸው፤


فِي جَنَّـٰتِ ٱلنَّعِيمِ

በድሎት ገነቶች ውስጥ፡፡


عَلَىٰ سُرُرٖ مُّتَقَٰبِلِينَ

ፊት ለፊት የሚታያዩ ሲሆኑ በአልጋዎች ላይ (ይንፈላሰሳሉ)፡፡


يُطَافُ عَلَيۡهِم بِكَأۡسٖ مِّن مَّعِينِۭ

ከሚመነጭ ወይን ጠጅ በያዘ ብርጭቆ በእነርሱ ላይ ይዞርባቸዋል፡፡


بَيۡضَآءَ لَذَّةٖ لِّلشَّـٰرِبِينَ

ነጭ ለጠጪዎች ጣፋጭ ከኾነች፡፡


لَا فِيهَا غَوۡلٞ وَلَا هُمۡ عَنۡهَا يُنزَفُونَ

በእርሷ ውስጥም ምታት የለባትም፡፡ እነርሱም ከእርሷ የሚሰክሩ አይደሉም፡፡


وَعِندَهُمۡ قَٰصِرَٰتُ ٱلطَّرۡفِ عِينٞ

እነርሱም ዘንድ ዓይናቸውን (በባሎቻቸው ላይ) አሳጣሪዎች የኾኑ ዓይናማዎች አልሉ፡፡


كَأَنَّهُنَّ بَيۡضٞ مَّكۡنُونٞ

እነርሱ ልክ የተሸፈነ (የሰጎን) ዕንቁላል ይመስላሉ፡፡



الصفحة التالية
Icon