إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ

እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡


إِنَّهُۥ مِنۡ عِبَادِنَا ٱلۡمُؤۡمِنِينَ

እርሱ ከምእምናን ባሮቻችን ነውና፡፡


ثُمَّ أَغۡرَقۡنَا ٱلۡأٓخَرِينَ

ከዚያም ሌሎቹን አሰጠምን፡፡


۞وَإِنَّ مِن شِيعَتِهِۦ لَإِبۡرَٰهِيمَ

ኢብራሂምም በእርግጥ ከተከታዮቹ ነው፡፡


إِذۡ جَآءَ رَبَّهُۥ بِقَلۡبٖ سَلِيمٍ

ወደ ጌታው በቅን ልብ በመጣ ጊዜ (የኾነውን አስታውስ)፡፡፡


إِذۡ قَالَ لِأَبِيهِ وَقَوۡمِهِۦ مَاذَا تَعۡبُدُونَ

«ለአባቱና ለሕዝቦቹ ምንን ትግገዛላችሁ?» ባለ ጊዜ፡፡


أَئِفۡكًا ءَالِهَةٗ دُونَ ٱللَّهِ تُرِيدُونَ

«ለቅጥፈት ብላችሁ ከአላህ ሌላ አማልክትን ትሻላችሁን?


فَمَا ظَنُّكُم بِرَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ

«በዓለማትም ጌታ ሃሳባችሁ ምንድን ነው?» አለ፡፡


فَنَظَرَ نَظۡرَةٗ فِي ٱلنُّجُومِ

በከዋክብትም መመልከትን ተመለከተ፡፡


فَقَالَ إِنِّي سَقِيمٞ

«እኔ በሽተኛ ነኝም» አለ፡፡


فَتَوَلَّوۡاْ عَنۡهُ مُدۡبِرِينَ

ከእርሱም የሸሹ ሆነው ኼዱ፡፡



الصفحة التالية
Icon