أَلَآ إِنَّهُم مِّنۡ إِفۡكِهِمۡ لَيَقُولُونَ

ንቁ! እነርሱ ከቅጥፈታቸው (የተነሳ) ይላሉ፡-


وَلَدَ ٱللَّهُ وَإِنَّهُمۡ لَكَٰذِبُونَ

«አላህ (መላእክትን) ወለደ፡፡» እነርሱም በእርግጥ ውሸታሞች ናቸው፡፡


أَصۡطَفَى ٱلۡبَنَاتِ عَلَى ٱلۡبَنِينَ

በወንዶች ልጆች ላይ ይልቅ ሴቶችን ልጆች መረጥን?


مَا لَكُمۡ كَيۡفَ تَحۡكُمُونَ

ለእናንተ ምን (አስረጅ) አላችሁ? እንዴት ትፈርዳላችሁ!


أَفَلَا تَذَكَّرُونَ

አትገነዘቡምን?


أَمۡ لَكُمۡ سُلۡطَٰنٞ مُّبِينٞ

ወይስ ለእናንተ ግልጽ አስረጅ አላችሁን?


فَأۡتُواْ بِكِتَٰبِكُمۡ إِن كُنتُمۡ صَٰدِقِينَ

«እውነተኞች እንደ ሆናችሁ መጽሐፋችሁን አምጡ» (በላቸው)፡፡


وَجَعَلُواْ بَيۡنَهُۥ وَبَيۡنَ ٱلۡجِنَّةِ نَسَبٗاۚ وَلَقَدۡ عَلِمَتِ ٱلۡجِنَّةُ إِنَّهُمۡ لَمُحۡضَرُونَ

በአላህና በአጋንንት መካከልም ዝምድናን አደረጉ፡፡ አጋንንትም እነርሱ (ይህን ባዮች በእሳት) የሚጣዱ መሆናቸውን በእርግጥ ዐውቀዋል፡፡


سُبۡحَٰنَ ٱللَّهِ عَمَّا يَصِفُونَ

አላህ ከሚመጥኑት ሁሉ ጠራ፡፡


إِلَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلۡمُخۡلَصِينَ

ግን የተመረጡት የአላህ ባሮች (በአላህ ላይ አይዋሹም)፡፡



الصفحة التالية
Icon