فَإِنَّكُمۡ وَمَا تَعۡبُدُونَ

እናንተም የምትገዟቸውም ሁሉ፤


مَآ أَنتُمۡ عَلَيۡهِ بِفَٰتِنِينَ

በእርሱ (በአላህ) ላይ አንድንም አጥማሚዎች አይደላችሁም፡፡


إِلَّا مَنۡ هُوَ صَالِ ٱلۡجَحِيمِ

ያንን እርሱ ገሀነምን ገቢ የሆነውን ሰው ቢሆን እንጅ፡፡


وَمَامِنَّآ إِلَّا لَهُۥ مَقَامٞ مَّعۡلُومٞ

(ጂብሪል አለ) ከእኛም አንድም የለም፤ ለእርሱ የታወቀ ደረጃ ያለው ቢሆን እንጅ፡፡


وَإِنَّا لَنَحۡنُ ٱلصَّآفُّونَ

እኛም (ጌታን ለመግገዛት) ተሰላፊዎቹ እኛ ነን፡፡


وَإِنَّا لَنَحۡنُ ٱلۡمُسَبِّحُونَ

እኛም (አላህን) አጥሪዎቹ እኛ ነን፡፡


وَإِن كَانُواْ لَيَقُولُونَ

እነርሱም (ከሓዲዎቹ) በእርግጥ ይሉ ነበሩ፡-


لَوۡ أَنَّ عِندَنَا ذِكۡرٗا مِّنَ ٱلۡأَوَّلِينَ

«ከቀድሞዎቹ (መጻሕፍት) ገሳጭ መጽሐፍ እኛ ዘንድ በነበረን ኖሮ፤


لَكُنَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلۡمُخۡلَصِينَ

«የአላህ ምርጦች ባሮች በሆን ነበር፡፡»


فَكَفَرُواْ بِهِۦۖ فَسَوۡفَ يَعۡلَمُونَ

ግን (ቁርኣኑ በመጣላቸው ጊዜ) በእርሱ ካዱ፡፡ ወደፊትም በእርግጥ ያውቃሉ፡፡


وَلَقَدۡ سَبَقَتۡ كَلِمَتُنَا لِعِبَادِنَا ٱلۡمُرۡسَلِينَ

(የእርዳታ) ቃላችንም መልክተኞች ለሆኑት ባሮቻችን በእውነት አልፋለች፡፡



الصفحة التالية
Icon