وَأَعۡطَىٰ قَلِيلٗا وَأَكۡدَىٰٓ

ጥቂትን የሰጠውንና ያቋረጠውንም (አየህን?)


أَعِندَهُۥ عِلۡمُ ٱلۡغَيۡبِ فَهُوَ يَرَىٰٓ

የሩቁ ምስጢር ዕውቀት እርሱ ዘንድ አልለን? ስለዚህ እርሱ ያያልን?


أَمۡ لَمۡ يُنَبَّأۡ بِمَا فِي صُحُفِ مُوسَىٰ

ይልቁንም በዚያ በሙሳ ጽሑፎች ውስጥ ባለው ነገር አልተነገረምን?


وَإِبۡرَٰهِيمَ ٱلَّذِي وَفَّىٰٓ

በዚያም (የታዘዘውን) በፈጸመው በኢብራሂም (ጽሑፎች ውስጥ ባለው አልተነገረምን?)


أَلَّا تَزِرُ وَازِرَةٞ وِزۡرَ أُخۡرَىٰ

(እርሱም ኃጢያት) ተሸካሚ ነፍስ የሌላይቱን ነፍስ ኃጢኣት አትሸከምም፡፡


وَأَن لَّيۡسَ لِلۡإِنسَٰنِ إِلَّا مَا سَعَىٰ

ለሰውም ሁሉ የሠራው እንጅ ሌላ የለውም፡፡


وَأَنَّ سَعۡيَهُۥ سَوۡفَ يُرَىٰ

ሥራውም ሁሉ ወደ ፊት ይታያል፡፡


ثُمَّ يُجۡزَىٰهُ ٱلۡجَزَآءَ ٱلۡأَوۡفَىٰ

ከዚያም ሙሉውን ምንዳ ይመነዳዋል፡፡


وَأَنَّ إِلَىٰ رَبِّكَ ٱلۡمُنتَهَىٰ

መጨረሻውም ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡


وَأَنَّهُۥ هُوَ أَضۡحَكَ وَأَبۡكَىٰ

እነሆ እርሱም አስሳቀ፣ አስለቀሰም፡፡


وَأَنَّهُۥ هُوَ أَمَاتَ وَأَحۡيَا

እነሆ እርሱም ገደለ፣ አስነሳም፡፡



الصفحة التالية
Icon