إِنَّآ أَنشَأۡنَٰهُنَّ إِنشَآءٗ

እኛ አዲስ ፍጥረት አድርገን (ለእነርሱ) ፈጠርናቸው፡፡


فَجَعَلۡنَٰهُنَّ أَبۡكَارًا

ደናግሎችም አደረግናቸው፡፡


عُرُبًا أَتۡرَابٗا

ለባሎቻቸው ተሽሞርሟሪዎች እኩያዎች (አደረግናቸው)፡፡


لِّأَصۡحَٰبِ ٱلۡيَمِينِ

ለቀኝ ጓዶች (አዘጋጀናቸው)፡፡


ثُلَّةٞ مِّنَ ٱلۡأَوَّلِينَ

ከፊተኞቹ ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡


وَثُلَّةٞ مِّنَ ٱلۡأٓخِرِينَ

ከኋለኞቹም ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡


وَأَصۡحَٰبُ ٱلشِّمَالِ مَآ أَصۡحَٰبُ ٱلشِّمَالِ

የግራ ጓደኞችም ምንኛ (የተዋረዱ) የግራ ጓዶች! ናቸው፡፡


فِي سَمُومٖ وَحَمِيمٖ

በመርዛም ነፋስ በጣም በፈላ ውሃም ውስጥ ናቸው፡፡


وَظِلّٖ مِّن يَحۡمُومٖ

ከጥቁር ጭስም በኾነ ጥላ ውስጥ፡፡


لَّا بَارِدٖ وَلَا كَرِيمٍ

ቀዝቃዛም መልካምም ያልኾነ፡፡


إِنَّهُمۡ كَانُواْ قَبۡلَ ذَٰلِكَ مُتۡرَفِينَ

እነርሱ ከዚህ በፊት ቅምጥሎች ነበሩና፡፡


وَكَانُواْ يُصِرُّونَ عَلَى ٱلۡحِنثِ ٱلۡعَظِيمِ

በታላቅ ኀጢአትም ላይ ይዘወትሩ ነበሩና፡፡



الصفحة التالية
Icon