أَفَرَءَيۡتُمُ ٱلۡمَآءَ ٱلَّذِي تَشۡرَبُونَ

ያንንም የምትጠጡትን ውሃ አየችሁን?


ءَأَنتُمۡ أَنزَلۡتُمُوهُ مِنَ ٱلۡمُزۡنِ أَمۡ نَحۡنُ ٱلۡمُنزِلُونَ

እናንተ ከደመናው አወረዳችሁትን? ወይስ እኛ አውራጆቹ ነን?


لَوۡ نَشَآءُ جَعَلۡنَٰهُ أُجَاجٗا فَلَوۡلَا تَشۡكُرُونَ

ብንሻ ኖሮ መርጋጋ ባደረግነው ነበር፡፡ አታመሰግኑምን?


أَفَرَءَيۡتُمُ ٱلنَّارَ ٱلَّتِي تُورُونَ

ያቺንም የምትሰብቋትን እሳት አያችሁን?


ءَأَنتُمۡ أَنشَأۡتُمۡ شَجَرَتَهَآ أَمۡ نَحۡنُ ٱلۡمُنشِـُٔونَ

እናንተ ዛፏን ፈጠራችሁን? ወይስ እኛ ፈጣሪዎችዋ ነን?


نَحۡنُ جَعَلۡنَٰهَا تَذۡكِرَةٗ وَمَتَٰعٗا لِّلۡمُقۡوِينَ

እኛ (ለገሀናም) ማስታወሻ ለመንገደኞችም መጠቀሚያ አደረግናት፡፡


فَسَبِّحۡ بِٱسۡمِ رَبِّكَ ٱلۡعَظِيمِ

የታላቁን ጌታህንም ስም አወድስ፡፡


۞فَلَآ أُقۡسِمُ بِمَوَٰقِعِ ٱلنُّجُومِ

በከዋክብትም መጥለቂያዎች እምላለሁ፡፡


وَإِنَّهُۥ لَقَسَمٞ لَّوۡ تَعۡلَمُونَ عَظِيمٌ

እርሱም ብታወቁ ታላቅ መሓላ ነው፡፡


إِنَّهُۥ لَقُرۡءَانٞ كَرِيمٞ

እርሱ የከበረ ቁርኣን ነው፡፡



الصفحة التالية
Icon