فِي كِتَٰبٖ مَّكۡنُونٖ

በተጠበቀ መጽሐፍ ውስጥ ነው፡፡


لَّا يَمَسُّهُۥٓ إِلَّا ٱلۡمُطَهَّرُونَ

የተጥራሩት እንጅ ሌላ አይነካውም፡፡


تَنزِيلٞ مِّن رَّبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ

ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡


أَفَبِهَٰذَا ٱلۡحَدِيثِ أَنتُم مُّدۡهِنُونَ

በዚህ ንግግር እናንተ ቸልተኞች ናችሁን?


وَتَجۡعَلُونَ رِزۡقَكُمۡ أَنَّكُمۡ تُكَذِّبُونَ

ሲሳያችሁንም (ዝናምን) እናንተ የምታስተባብሉት ታደርጋላችሁን?


فَلَوۡلَآ إِذَا بَلَغَتِ ٱلۡحُلۡقُومَ

(ነፍስ) ጉረሮንም በደረሰች ጊዜ፡፡


وَأَنتُمۡ حِينَئِذٖ تَنظُرُونَ

እናንተ ያን ጊዜ የምታዩ ስትኾኑ፡፡


وَنَحۡنُ أَقۡرَبُ إِلَيۡهِ مِنكُمۡ وَلَٰكِن لَّا تُبۡصِرُونَ

እኛም ግን አታዩም እንጅ ከእናንተ ይልቅ ወደእርሱ የቀረብን ስንኾን፡፡


فَلَوۡلَآ إِن كُنتُمۡ غَيۡرَ مَدِينِينَ

የማትዳኙም ከኾናችሁ፡፡


تَرۡجِعُونَهَآ إِن كُنتُمۡ صَٰدِقِينَ

እውነተኞች እንደ ኾናችሁ (ነፍሲቱን ወደ አካሉ) ለምን አትመልሷትም፡፡


فَأَمَّآ إِن كَانَ مِنَ ٱلۡمُقَرَّبِينَ

(ሟቹ) ከባለሟሎቹ ቢኾንማ፡፡



الصفحة التالية
Icon