فَأَمَّا مَنۡ أُوتِيَ كِتَٰبَهُۥ بِيَمِينِهِۦ فَيَقُولُ هَآؤُمُ ٱقۡرَءُواْ كِتَٰبِيَهۡ

መጽሐፉን በቀኙ የተሰጠ ሰውማ (ለጓደኞቹ) «እንኩ፤ መጽሐፌን አንብቡ» ይላል፡፡


إِنِّي ظَنَنتُ أَنِّي مُلَٰقٍ حِسَابِيَهۡ

«እኔ ምርመራየን የምገናኝ መኾኔን አረጋገጥኩ፤» (ተዘጋጀሁም ይላል)፡፡


فَهُوَ فِي عِيشَةٖ رَّاضِيَةٖ

እርሱም በተወደደች ኑሮ ውሰጥ ይኾናል፡፡


فِي جَنَّةٍ عَالِيَةٖ

በከፍተኛይቱ ገነት ውስጥ፡፡


قُطُوفُهَا دَانِيَةٞ

ፍሬዎችዋ ቅርቦች የኾኑ፡፡


كُلُواْ وَٱشۡرَبُواْ هَنِيٓـَٔۢا بِمَآ أَسۡلَفۡتُمۡ فِي ٱلۡأَيَّامِ ٱلۡخَالِيَةِ

በአለፉት ቀናት ውስጥ (በምድረ ዓለም) ባስቀደማችሁት ምክንያት ብሉ፤ ጠጡም፤ (ይባላሉ)፡፡


وَأَمَّا مَنۡ أُوتِيَ كِتَٰبَهُۥ بِشِمَالِهِۦ فَيَقُولُ يَٰلَيۡتَنِي لَمۡ أُوتَ كِتَٰبِيَهۡ

መጽሐፉንም በግራው የተሰጠማ «ዋ ጥፋቴ! ምነው መጽሐፌን ባልተሰጠሁ» ይላል፡፡


وَلَمۡ أَدۡرِ مَا حِسَابِيَهۡ

«ምርመራየንም ምን እንደኾነ ባላወቅኩ፡፡


يَٰلَيۡتَهَا كَانَتِ ٱلۡقَاضِيَةَ

«እርሷ (ሞት ሕይወቴን) ምነው ፈጻሚ በኾነች፡፡


مَآ أَغۡنَىٰ عَنِّي مَالِيَهۡۜ

«ገንዘቤ ከእኔ ምንንም አላብቃቃኝ፤ (አልጠቀመኝም)፡፡



الصفحة التالية
Icon