إِنَّهُۥ لَقَوۡلُ رَسُولٖ كَرِيمٖ

እርሱ (ቁርኣን) የተከበረ መልክተኛ ቃል ነው፡፡


وَمَا هُوَ بِقَوۡلِ شَاعِرٖۚ قَلِيلٗا مَّا تُؤۡمِنُونَ

እርሱም የባለቅኔ ቃል (ግጥም) አይደለም፡፡ ጥቂትን ብቻ ታምናላችሁ፡፡


وَلَا بِقَوۡلِ كَاهِنٖۚ قَلِيلٗا مَّا تَذَكَّرُونَ

የጠንቋይም ቃል አይደለም፡፡ ጥቂትን ብቻ ታስታውሳላችሁ፡፡


تَنزِيلٞ مِّن رَّبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ

ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡


وَلَوۡ تَقَوَّلَ عَلَيۡنَا بَعۡضَ ٱلۡأَقَاوِيلِ

በእኛ ላይም ከፊልን ቃላት (ያላልነውን) በቀጠፈ ኖሮ፤


لَأَخَذۡنَا مِنۡهُ بِٱلۡيَمِينِ

በኀይል በያዝነው ነበር፡፡


ثُمَّ لَقَطَعۡنَا مِنۡهُ ٱلۡوَتِينَ

ከዚያም ከእርሱ የልቡን ሥር (የተንጠለጠለበትን ጅማት) በቆረጥን ነበር፡፡


فَمَا مِنكُم مِّنۡ أَحَدٍ عَنۡهُ حَٰجِزِينَ

ከእናንተም ውስጥ ከእርሱ ላይ ከልካዮች ምንም አይኖሩም፡፡


وَإِنَّهُۥ لَتَذۡكِرَةٞ لِّلۡمُتَّقِينَ

እርሱም (ቁርኣን) ለጥንቁቆቹ መገሠጫ ነው፡፡


وَإِنَّا لَنَعۡلَمُ أَنَّ مِنكُم مُّكَذِّبِينَ

እኛም ከእናንተ ውስጥ አስተባባዮች መኖራቸውን በእርግጥ እናውቃለን፡፡



الصفحة التالية
Icon