يُبَصَّرُونَهُمۡۚ يَوَدُّ ٱلۡمُجۡرِمُ لَوۡ يَفۡتَدِي مِنۡ عَذَابِ يَوۡمِئِذِۭ بِبَنِيهِ

(ዘመዶቻቸውን) ያዩዋቸዋል፡፡ አመጸኛው ከዚያ ቀን ስቃይ (ነፍሱን) በልጆቹ ሊበዥ ይመኛል፡፡


وَصَٰحِبَتِهِۦ وَأَخِيهِ

በሚስቱም በወንድሙም፡፡


وَفَصِيلَتِهِ ٱلَّتِي تُـٔۡوِيهِ

በዚያችም በምታስጠጋው ጎሳው፡፡


وَمَن فِي ٱلۡأَرۡضِ جَمِيعٗا ثُمَّ يُنجِيهِ

በምድርም ላይ ባለው ሁሉ (ሊበዥ) ከዚያም ሊያድነው (ይመኛል)፡፡


كَلَّآۖ إِنَّهَا لَظَىٰ

ይተው! እርሷ (እሳቲቱ) ለዟ ናት፡፡


نَزَّاعَةٗ لِّلشَّوَىٰ

የራስን ቅል ቆዳ የምትሞሽልቅ ስትኾን፡፡


تَدۡعُواْ مَنۡ أَدۡبَرَ وَتَوَلَّىٰ

(ከእምነት) የዞረንና የሸሸን ሰው (ወደእርሷ) ትጠራለች፡፡


وَجَمَعَ فَأَوۡعَىٰٓ

ገንዘብን የሰበሰበንና (ዘካውን ሳይሰጥ) የቆጠረንም፤ (ትጠራለች)፡፡


۞إِنَّ ٱلۡإِنسَٰنَ خُلِقَ هَلُوعًا

ሰው ቅጠ ቢስ ኾኖ ተፈጠረ፡፡


إِذَا مَسَّهُ ٱلشَّرُّ جَزُوعٗا

ክፉ ነገር ባገኘው ጊዜ ብስጪተኛ፡፡


وَإِذَا مَسَّهُ ٱلۡخَيۡرُ مَنُوعًا

መልካምም ነገር (ድሎት) ባገኘ ጊዜ ከልካይ (ኾኖ ተፈጠረ)፡፡



الصفحة التالية
Icon