كَلَّا لَا وَزَرَ

ይከልከል፤ ምንም መጠጊያ የለም፡፡


إِلَىٰ رَبِّكَ يَوۡمَئِذٍ ٱلۡمُسۡتَقَرُّ

በዚያ ቀን መርጊያው ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡


يُنَبَّؤُاْ ٱلۡإِنسَٰنُ يَوۡمَئِذِۭ بِمَا قَدَّمَ وَأَخَّرَ

ሰው በዚያ ቀን ባስቀደመውና ባስቆየው ሁሉ ይነገራል፡፡


بَلِ ٱلۡإِنسَٰنُ عَلَىٰ نَفۡسِهِۦ بَصِيرَةٞ

በእርግጥም ሰው በነፍሱ ላይ አስረጅ ነው፡፡ (አካሎቹ ይመሰክሩበታል)፡፡


وَلَوۡ أَلۡقَىٰ مَعَاذِيرَهُۥ

ምክንያቶቹን ሁሉ ቢያመጣም እንኳ (አይሰማም)፡፡


لَا تُحَرِّكۡ بِهِۦ لِسَانَكَ لِتَعۡجَلَ بِهِۦٓ

በእርሱ (በቁርኣን ንባብ) ልትቸኩል ምላስህን በእርሱ አታላውስ፡፡


إِنَّ عَلَيۡنَا جَمۡعَهُۥ وَقُرۡءَانَهُۥ

(በልብህ ውስጥ) መሰብሰቡና ማንበቡ በእኛ ላይ ነውና፡፡


فَإِذَا قَرَأۡنَٰهُ فَٱتَّبِعۡ قُرۡءَانَهُۥ

ባነበብነውም ጊዜ (ካለቀ በኋላ) ንባቡን ተከተል፡፡


ثُمَّ إِنَّ عَلَيۡنَا بَيَانَهُۥ

ከዚያም ማብራራቱ በእኛ ላይ ነው፡፡


كَلَّا بَلۡ تُحِبُّونَ ٱلۡعَاجِلَةَ

(ከመጣደፍ) ተከልከል፡፡ ይልቁንም (ሰዎች) ፈጣኒቱን (ዓለም) ትወዳላችሁ፡፡


وَتَذَرُونَ ٱلۡأٓخِرَةَ

መጨረሻይቱንም (ዓለም) ትተዋላችሁ፡፡ (አትዘጋጁላትም)፡፡



الصفحة التالية
Icon